ነፍሴ በእጁ በሆነው እምላለሁ እኔ ከአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሶላት ጋር ለመመሳሰል እጅግ የቀረበውን ሶላት የምሰግድ ነኝ። ዱንያን እስኪለያዩ ድረስ ይህቺው ነበረች አሰጋገዳቸው።
ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: አቡ ሁረይራ ግዴታ ሶላቶችም ሆኑ ሱና ሶላቶች በረመዳን ውስጥም ሆነ በሌላ ወቅት በሁሉም ሶላቶች ሲሰግድ ተክቢራ ያደርግ ነበር። በሚቆም ጊዜ ተክቢራ ያደርጋል፤ ከዚያም ሩኩዕ በሚያደርግ ጊዜ ተክቢራ ያደርጋል፤ ከዚያም "ሰሚዐሏሁ ሊመን ሐሚደህ" "አላህ ላመሰገነው ሰው ሰሚ ነው።" ይላል፤ ከዚያም ሱጁድ ከመውረዱ በፊትም "ረበና ወለከል…

