'ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከሁሉም ግዴታ ሶላቶች በኋላ እንዲህ ይሉ ነበር
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
የሙጊራ ቢን ሹዕባ ጸሐፊ ከሆነው ወራድ እንደተላለፈው እንዲህ አለ: "ሙጊራ ቢን ሹዕባ ወደ ሙዐዊያህ የሚጻፍን እንዲህ የሚል ደብዳቤ አጻፈኝ: 'ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከሁሉም ግዴታ ሶላቶች በኋላ እንዲህ ይሉ ነበር ‹ላኢላሀ ኢለሏሁ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለህ፤ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዓላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር፤ አላሁመ ላማኒዐ ሊማ አዕጦይተ ወላሙዕጢየ ሊማ መነዕተ ወላ የንፈዑ ዘልጀዲ ሚንከልጀድ› ትርጉሙም 'ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም። ብቸኛና ለርሱ አጋር የሌለው ነው። ንግስናም ምስጋናም ለርሱ ነው። እርሱ በሁሉ ነገር ላይ ቻይ ነው። አላህ ሆይ! ለሰጠኸው ማንም ከልካይ የለውም። ለከለከልከውም ማንም ሰጪ የለውም። የክብር ባለቤትም ክብሩ ካንተ (ቅጣት) አያድንም።'"
Explanation
ማለትም: የተውሒድ ቃል በሆነችው "ላኢላሀ ኢለሏህ" አረጋግጣለሁም አምናለሁም። ትክክለኛዋን አምልኮም ለአላህ አፅንቼ ከርሱ ውጪ ካሉ አካላቶችም ውድቅ አደርጋታለሁ። ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ የለም። እውነተኛውና የተሟላው ንግስና፣ የሰማያትና የምድር ባለቤቶችም ምስጋና ሁሉ ለአላህ የተገባ መሆኑን አረጋግጣለሁ። እርሱም በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው። አላህ የወሰነው መስጠትም ይሁን መከልከል ማንም መላሽ የለውም። እርሱ ዘንድ የሀብት ባለቤት ሀብቱ አይጠቅመውም። ብቸኛ የሚጠቅመው መልካም ስራ ነው።
Benefits
ሱናን ወደ መተግበርና ማሰራጨት መቻኮል እንደሚገባ እንረዳለን።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

