አላህን በጠየቃችሁ ጊዜ ፊርደውስን ጠይቁት።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከዑባዳህ ቢን ሷሚት (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ ብለዋል: "ጀነት ውስጥ መቶ ደረጃዎች አሉ። በየሁሉም ደረጃዎች መካከል በሰማይና በምድር መካከል ያለውን ርቀት ያህል አለ። ፊርደውስ የላይኛው ደረጃ ነው። የጀነት ወንዞች የሚመነጩትም ከርሷ ነው። ከላዩዋ ያለውም (ጣሪያዋ) ዐርሽ ነው። አላህን በጠየቃችሁ ጊዜ ፊርደውስን ጠይቁት።"
Explanation
Benefits
አላህን ከጀነት ሁሉ ላእላይ የሆነችውን ፊርደውስ እንድንጠይቀው መነሳሳቱን እንረዳለን።
ፊርደውስ የጀነት ላይኛዋና በላጯ እንደሆነች እንረዳለን።
ሙስሊም የሆነ ሰው ከፍ ያለ አላማ ሊኖረው እንደሚገባና አላህ ዘንድ የላቀ የሆነንና በላጭ የሆነን ደረጃ ለማግኘት መልፋትና መጣር እንደሚገባው እንረዳለን።
ጀነት አራት ወንዞች አሏት: እነርሱም: የውሃ፣ የወተት፣ ወይን ጠጅና የማር ናቸው። እነዚህም በዚህ የአላህ ንግግር ውስጥ በቁርአን ተጠቅሰዋል። {የዚያች ጥንቁቆች ተስፋ የተሰጧት ጀነት ምሳሌ በውስጧ ሽታውን ከማይለውጥ ውሃ ወንዞች፣ ጣዕሙ ከማይለወጥ ወተትም ወንዞች፣ ለጠጪዎች ሁሉ ጣፋጭ ከሆነች የወይን ጠጅም ወንዞች፣ ከተነጠረ ማርም ወንዞች አልሉባት።} [ሙሐመድ: 15]
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

