የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ሱጁድ ውስጥ እንዲህ ይሉ ነበር "አላሁመግፊርሊ ዘንቢ ኩለሁ ዲቀሁ ወጂለሁ፣ ወአወለሁ ወአኺረሁ፣ ወዐላኒየተሁ ወሲረሁ"» ትርጉሙም "አላህ ሆይ! ደቂቁንም ትልቁንም፣ የመጀመሪያውንም የመጨረሻውንም፣ ግልፁንም፣ ድብቁንም ወንጀሌን ሁሉንም ማረኝ።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: «የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ሱጁድ ውስጥ እንዲህ ይሉ ነበር "አላሁመግፊርሊ ዘንቢ ኩለሁ ዲቀሁ ወጂለሁ፣ ወአወለሁ ወአኺረሁ፣ ወዐላኒየተሁ ወሲረሁ"» ትርጉሙም "አላህ ሆይ! ደቂቁንም ትልቁንም፣ የመጀመሪያውንም የመጨረሻውንም፣ ግልፁንም፣ ድብቁንም ወንጀሌን ሁሉንም ማረኝ።"
Explanation
Benefits
(ደቂቁንም) የሚለውን (ትልቁንም) ከሚለው ያስቀደሙት ጠያቂው ጥያቄውን ቀስ በቀስ እንዲወጣና እንዲያሳድግ ነው። ሌላው ምክንያትም ብዙ ጊዜ ትላልቅ ወንጀሎች የሚከሰቱት በትናንሽ ወንጀሎች ላይ በመዘውተርና ትኩረት ባለመስጠት ነው። ትናንሽ ወንጀሎች ወደ ትላልቅ ወንጀሎች ያደርሳሉ። ወደ አንድ ነገር የሚያደርሱ ነገሮች ደግሞ በማፅደቅም ይሁን በማስወገድ ረገድ መቀደማቸው የተገባ ነው።
ከትናንሹም ከትላልቁም ከሁሉም ወንጀሎች ምህረትን በመፈለግ ወደ አላህ መዋደቅ ተገቢ ነው።
ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ ዱዓ ስናደርግ ማጠንከርና አንዱ ቃል ከአንዱ ቃል ቢያብቃቃን እንኳ ቃላቶችን ማብዛት እንደሚገባ ያስረዳናል።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

