'ላኢላሃ ኢለሏህ ወሕደሁ ላሸሪከ ለህ፤ አሏሁ አክበር ከቢራ፣ ወልሐምዱሊላሂ ከሢራ፣ ወሱብሓነሏሂ ረቢል ዓለሚን፣ ላሐውለ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላሂል ዐዚዚል ሐኪም በል።' አሉት።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከሰዕድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "አንድ የገጠር ሰው ወደ የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በመምጣት እንዲህ አለ: 'የምለውን ቃላት አስተምሩኝ?' እርሳቸውም 'ላኢላሃ ኢለሏህ ወሕደሁ ላሸሪከ ለህ፤ አሏሁ አክበር ከቢራ፣ ወልሐምዱሊላሂ ከሢራ፣ ወሱብሓነሏሂ ረቢል ዓለሚን፣ ላሐውለ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላሂል ዐዚዚል ሐኪም በል።' አሉት። (ትርጉሙም: ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ የለም፤ ብቸኛና አጋር የሌለው ነው። አላህ እጅግ ታላቅ ነው፤ ለአላህ ብዙ ምስጋና የተገባው ነው፤ የዓለማቱ ጌታ አላህ ጥራት የተገባው ነው፤ አሸናፊና ጥበበኛ ከሆነው ከአላህ በቀር ሀይልም ብልሀትም የለም።) እርሱም 'እነዚህ ቃላት ጌታዬን (የማወድስበት) ናቸው። ለኔስ (የምለምንበት)?' አላቸው። እርሳቸውም 'አላሁመጝፊር ሊ ወርሐምኒ ወህዲኒ ወርዙቅኒ። በል!' አሉት።" (ትርጉሙም: አላህ ሆይ! ማረኝ፣ እዘንልኝ፣ ምራኝ፣ ሲሳይን ለግሰኝ።)
Explanation
Benefits
ከዱዓእ በፊት አላህን ማውሳትና ማወደስ እንደሚወደድ እንረዳለን።
የሰው ልጅ በምርጥ ዱዓ፣ በቁርአንና በሐዲሥ በመጡ ዱንያዊና አኺራዊ መልካም ነገሮችን የሰበሰቡ በሆኑ ዱዓዎች ማድረጉ እንደሚወደድ እንረዳለን። በፈለገው ዱዓ ማድረግም ይችላል።
አንድ ባሪያ ለዱንያውና አኺራው የሚጠቅመውን ነገር በመማር ላይ መጓጓት ይገባዋል።
ምህረትን፣ እዝነትንና ሲሳይን በመፈለግ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን። እነዚህ ጉዳዮችም የመልካም ነገሮች መሰብሰቢያ ናቸው።
ነቢዩ ( የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለኡመታቸው የሚጠቅማቸውን ነገር በማስተማር ላይ መራራታቸውን እንረዳለን።
ከምህረት መለመን በኋላ እዝነትን መለመን የተወሳው ንፅህናው እንዲሟላ ነው። ምህረት ማለት ወንጀልህ መሸሸጉ፣ መታበሱና ከእሳት መዳን ሲሆን እዝነት ደግሞ መልካምን ማግኘትና ጀነት መግባት ነው። ትልቁ ስኬት ይህ ነው።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

