አልላሁመ ለከ አስለምቱ፣ ወቢከ አመንቱ፣ ወዐለይከ ተወከልቱ፣ ወኢለይከ አነብቱ፣ ወቢከ ኻሶምቱ፤ አልላሁመ ኢኒ አዑዙ ቢዒዘቲከ፣ ላኢላሃ ኢላ አንተ አንቱዲለኒ፣ አንተልሐይዩ ለዚ ላየሙት፣ ወልጂኑ ወልኢንሱ የሙቱን" ትርጉሙም "አላህ ሆይ! ላንተ እጅ ሰጥቻለሁ፤ ባንተም አምኛለሁ፤ ባንተም ላይ ተመክቻለሁ፤ ወዳንተም ተመልሻለሁ፤ ባንተ መንገድም ተሟግቻለሁ፤ አላህ ሆይ! እኔ እንዳታጠመኝ በልቅናህ እጠበቃለሁ፤ ካንተ በቀርም በእውነት የሚመለክ የለም። የማይሞት ህያው አንተው ነህ። ጋኔንም ሰውም ይሞታሉ።" ማለት ነው።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከኢብኑ ዓባስ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ ይሉ ነበር: "አልላሁመ ለከ አስለምቱ፣ ወቢከ አመንቱ፣ ወዐለይከ ተወከልቱ፣ ወኢለይከ አነብቱ፣ ወቢከ ኻሶምቱ፤ አልላሁመ ኢኒ አዑዙ ቢዒዘቲከ፣ ላኢላሃ ኢላ አንተ አንቱዲለኒ፣ አንተልሐይዩ ለዚ ላየሙት፣ ወልጂኑ ወልኢንሱ የሙቱን" ትርጉሙም "አላህ ሆይ! ላንተ እጅ ሰጥቻለሁ፤ ባንተም አምኛለሁ፤ ባንተም ላይ ተመክቻለሁ፤ ወዳንተም ተመልሻለሁ፤ ባንተ መንገድም ተሟግቻለሁ፤ አላህ ሆይ! እኔ እንዳታጠመኝ በልቅናህ እጠበቃለሁ፤ ካንተ በቀርም በእውነት የሚመለክ የለም። የማይሞት ህያው አንተው ነህ። ጋኔንም ሰውም ይሞታሉ።" ማለት ነው።
Explanation
Benefits
በአላህ ላይ ብቻ መመካትና ከርሱ ጥበቃን መፈለግ ግዴታ እንደሆነ እንረዳለን። ምክንያቱም እርሱ በምሉዕነት መገለጫዎች የሚገለፅ ነውና። እርሱ ብቻ ነው መጠጊያ። ፍጡራን ባጠቃላይ ደካሞችና ሞት የሚከተላቸው ናቸው። ስለዚህም በነርሱ ላይ ለመመካት ብቁ አይደሉም።
ሁሉን ያቀፉና ምንም ያላስቀሩ በሆኑት እንዲሁም እውነተኛ ኢማንና ወሰን የለሽ እርግጠኝነትን የሚገልፁ በሆኑት በነዚህ ቃላቶች ዱዓ በማድረግ የነቢዩን (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ፈለግ መከተል ተገቢ እንደሆነ እንረዳለን።
ሲንዲይ እንዲህ ብለዋል: "(ህያው አንተው ነህ) ማለታቸው ጥበቃ ሊፈለግበት የሚገባው አንተ ብቻ እንጂ ሌላ ማንም አይደለም። ለማለት ነው።"
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

