አንድ ሰው ወደ ቤቱ ሲገባ በሚገባበት ወቅትም በሚበላበት ወቅትም አላህን ካወሳ ሰይጣን (ለባልደረቦቹ) 'ማደሪያም እራትም የላችሁም።' ይላል።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከጃቢር ቢን ዐብደላህ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እርሱ ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ሲሉ ሰማ: "አንድ ሰው ወደ ቤቱ ሲገባ በሚገባበት ወቅትም በሚበላበት ወቅትም አላህን ካወሳ ሰይጣን (ለባልደረቦቹ) 'ማደሪያም እራትም የላችሁም።' ይላል። በሚገባ ወቅት አላህን ሳያወሳ የገባ እንደሁ ሰይጣን 'ማደሪያ አግኝታችኋል' ይላል። በሚበላበት ወቅትም አላህን ካላወሳ ደግሞ 'ማደሪያም እራትም አግኝታችኋል።' ይላል።"
Explanation
Benefits
ሰይጣን የሰውን ልጅ በስራው፣ በእንቅስቃሴውና በሁሉም ጉዳዩ ይጠባበቀዋል። ሰው ከዚክር (ከውዳሴ) በተዘናጋ ጊዜ ሸይጧንም ከርሱ የሚፈልገው ፍላጎቱን ያገኛል።
ዚክር (ውዳሴ) ሰይጣንን እንደሚያባርር እንረዳለን።
ሁሉም ሰይጣን በንግግሩ የሚደሰቱና ትእዛዙን የሚከተሉት ተከታይና ወዳጆች እንዳሉት እንረዳለን።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

