افتتاح البرنامج الدعوي السبت القادم، ٩ / ٣ / ١٤٤٨هـ بعد صلاة الفجر مباشرة مسجد محمد بن إبراهيم، الجامعة الإسلامية بالمدينة المنورة فضيلة الشيخ د. هيثم بن محمد سرحان دورة اليوم الواحد، وختم كتاب كل سبت بإذن الله حياكم الله ونفع بكم. افتتاح البرنامج الدعوي السبت القادم، ٩ / ٣ / ١٤٤٨هـ بعد صلاة الفجر مباشرة مسجد محمد بن إبراهيم، الجامعة الإسلامية بالمدينة المنورة فضيلة الشيخ د. هيثم بن محمد سرحان دورة اليوم الواحد، وختم كتاب كل سبت بإذن الله حياكم الله ونفع بكم. افتتاح البرنامج الدعوي السبت القادم، ٩ / ٣ / ١٤٤٨هـ بعد صلاة الفجر مباشرة مسجد محمد بن إبراهيم، الجامعة الإسلامية بالمدينة المنورة فضيلة الشيخ د. هيثم بن محمد سرحان دورة اليوم الواحد، وختم كتاب كل سبت بإذن الله حياكم الله ونفع بكم. افتتاح البرنامج الدعوي السبت القادم، ٩ / ٣ / ١٤٤٨هـ بعد صلاة الفجر مباشرة مسجد محمد بن إبراهيم، الجامعة الإسلامية بالمدينة المنورة فضيلة الشيخ د. هيثم بن محمد سرحان دورة اليوم الواحد، وختم كتاب كل سبت بإذن الله حياكم الله ونفع بكم. افتتاح البرنامج الدعوي السبت القادم، ٩ / ٣ / ١٤٤٨هـ بعد صلاة الفجر مباشرة مسجد محمد بن إبراهيم، الجامعة الإسلامية بالمدينة المنورة فضيلة الشيخ د. هيثم بن محمد سرحان دورة اليوم الواحد، وختم كتاب كل سبت بإذن الله حياكم الله ونفع بكم. افتتاح البرنامج الدعوي السبت القادم، ٩ / ٣ / ١٤٤٨هـ بعد صلاة الفجر مباشرة مسجد محمد بن إبراهيم، الجامعة الإسلامية بالمدينة المنورة فضيلة الشيخ د. هيثم بن محمد سرحان دورة اليوم الواحد، وختم كتاب كل سبت بإذن الله حياكم الله ونفع بكم. افتتاح البرنامج الدعوي السبت القادم، ٩ / ٣ / ١٤٤٨هـ بعد صلاة الفجر مباشرة مسجد محمد بن إبراهيم، الجامعة الإسلامية بالمدينة المنورة فضيلة الشيخ د. هيثم بن محمد سرحان دورة اليوم الواحد، وختم كتاب كل سبت بإذن الله حياكم الله ونفع بكم. افتتاح البرنامج الدعوي السبت القادم، ٩ / ٣ / ١٤٤٨هـ بعد صلاة الفجر مباشرة مسجد محمد بن إبراهيم، الجامعة الإسلامية بالمدينة المنورة فضيلة الشيخ د. هيثم بن محمد سرحان دورة اليوم الواحد، وختم كتاب كل سبت بإذن الله حياكم الله ونفع بكم.
#3731[ሶሒሕ ነው።]
HadeethEnc · 1.23.0

አንዳችሁ የተኛ ጊዜ በማጅራቱ ላይ ሸይጧን ሶስት ቋጠሮ ይቋጥራል። በየሁሉም ቋጠሮ ላይም ረጅም ሌሊት አለና ተኛ! እያለ ይመታል።

Available translations

Choose an available translation of this Hadeeth

01

Hadeeth text

ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፦ "አንዳችሁ የተኛ ጊዜ በማጅራቱ ላይ ሸይጧን ሶስት ቋጠሮ ይቋጥራል። በየሁሉም ቋጠሮ ላይም ረጅም ሌሊት አለና ተኛ! እያለ ይመታል። ከነቃና አላህን ካወሳ አንዱ ቋጠሮ ይፈታል። ዉዱእ ካደረገ አንዱ ቋጠሮ ይፈታል። ከሰገደ ደግሞ አንዱ ቋጠሮ ይፈታል። ያኔ ንቁና ነፍሱ የተደሰተች ሆኖ ያነጋል። ያለበለዚያ ግን ነፍሱ የከበደችውና የሰነፈ ሆኖ ያነጋል።"
02

Explanation

ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ሸይጧን ሌሊት ለመስገድ ወይም ፈጅርን ለመስገድ መቆም ከፈለገ ሰው ጋር ያለውን ሁኔታና ግብግብ ነገሩን።

አማኝ ለመተኛት የሄደ ጊዜ ሸይጧን ማጅራቱ ላይ ሶስት ቋጠሮ ይቋጥርበታል።

አማኙ ነቅቶ አላህን ካወሳና ለሸይጧን ጉትጎታ እጅ ካልሰጠ አንዷ ቋጠሮ ትፈታለች።

ዉዱእ ካደረገ ደሞ ሌላኛዋ ቋጠሮ ትፈታለች

ቆሞ ከሰገደ ሶስተኛው ቋጠሮ ይፈታል። የሸይጧን ቋጠሮና ማዳከም ከመወገዱ በተጨማሪ አላህ ለአምልኮ ስለገጠመው በመደሰትና አላህ ቃል በገባለት ምንዳና ምህረት በመበሰር ንቁና ነፍሱም የተደሰተች ይሆናል። ያለበለዚያ ግን ነፍሱ የከበደችው፣ ቀልቡ ያዘነና ከመልካምና በጎ ስራ የተሳነፈ ይሆናል። ምክንያቱም እርሱ በሸይጧን ገመድ የታሰረና ወደ አር‐ራሕማን ከመቅረብ የራቀ ስለሆነ ነው።
03

Benefits

ሸይጧን ሁልጊዜ የሰው ልጅ መንገድ ላይ በርሱና አሸናፊና ታላቅ በሆነው አላህ አምልኮ መካከል ግርዶ ለማድረግ እንደሚለፋ እንረዳለን። አንድ ባሪያ በአላህ እስካልታገዘና ከርሱ መጠበቂያ ሰበቦችን እስካለወተጠቀመ ድረስም ከሸይጧን መዳኛ የለውም።
አላህን ማውሳትና ማምለክ ለነፍስ ንቃትን፣ የልብ ስፋትን ያወርሳል፤ ስንፍናና ደካማነትን ያባራል፤ ችግርና ጥላቻን ያስወግዳል። ምክንያቱም ሸይጧንን ያባርራልና። እነዚህ ነገሮች ደግሞ ከርሱ ጉትጎታዎች መካከል ስለሆኑ ነው።
አማኝ የሆነ ሰው አላህ ለርሱ አምልኮን በመግጠሙ ይደሰታል። ከሙሉና ላቅ ካለ ደረጃ በማጓደሉም ያዝናል።
ከአምልኮ መዘናጋትና መዘንበል የሸይጧን ተግባርና ማታለያ ነው።
አላህን ማውሳት፣ ዉዱእና ሶላት እነዚህ ሶስት ነገሮች ሸይጧንን ያባርራሉ።
ሸይጧን በተለየ መልኩ ማጅራት ላይ መቋጠሩ ይህ ቦታ የሀይል ማዕከልና የእንቅስቃሴ መስክ ስለሆነ ነው። እዚህ ቦታ ላይ ካሰረ የሰውን ልጅ ነፍስ መቆጣጠርና እንቅልፍ እርሱ ላይ መጣል ይመቸዋል።
ኢብኑ ሐጀር አልዐስቀላኒ እንዲህ ብለዋል: «"ላንተ ረጅም ሌሊት አለልህ።" በሚለው የሐዲሡ ክፍል ሌሊት መጠቀሱ በግልፅ የሚያስረዳን ይህ የሸይጧን ቋጠሮ ምሽት ላይ በሚተኛ እንቅልፍ ብቻ መሆኑን ነው።"
ኢብኑ ሐጀር አልዐስቀላኒ እንዲህ ብለዋል: «ዚክር ሲባል ሌላው አያብቃቃም በሚያስብል መልኩ የተለየ ዚክር መሆኑ ግድ አይደለም። ይልቁኑም አላህን ማውሳት የሚባል ነገርን ሁሉ ማለቱ ያብቃቃል። በመሆኑም ቁርአን ማንበብ፣ የነቢዩን ሐዲሥ ማንበብ፣ በሸሪዓዊ እውቀት መጠመድ እዚህ ውስጥ ይካተታል። አላህን ቢያወሳበት በላጭ የሆነው ዚክር ግን ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ሌሊት ላይ የነቃ ሰው እንዲል የተናገሩትን ዚክር ማለት ነው፤ እንዲህ ብለዋል: ("ላኢላሃ ኢለሏህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምድ ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር አልሐምዱ ሊላህ ወሱብሓነላህ ወላኢላሃ ኢለላህ ወላሁ አክበር ወላሐውለ ወላቁወተ ኢላ ቢላህ" ቀጥሎም እንዲህ አሉ: "አልላሁመግፊርሊ" ወይም ማንኛውም ዱዓ ካደረገ ተቀባይነት ይኖረዋል፤ ዉዱእ አድርጎ ከሰገደም ሶላቱ ተቀባይነት ይኖረዋል።) ቡኻሪ ዘግበውታል።

Attribution

[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

Categories

Share

Share hadeeth

Sharing options · 0 Total shares

Share

← Back to encyclopedia
Shopping Basket

Loading...