ሙስሊምን መስደብ አመፀኝነት ነው። መግደሉ ክህደት ነው።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከዐብደላህ ቢን መስዑድ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል: "ሙስሊምን መስደብ አመፀኝነት ነው። መግደሉ ክህደት ነው።"
Explanation
Benefits
ያለአግባብ ሙስሊምን የሚሳደብ ሰው መጨረሻው ከባድ እንደሆነ ተገልጿል። ያለአግባብ የሚሳደብ ሰው አመፀኛ ነውና።
ሙስሊምን መሳደብና መግደል ኢማንን ያደክመዋልም ያጎድለዋልም።
አንዳንድ ስራዎች ከእስልምና መንገድ ወደሚያስወጣው ትልቁ ክህደት ባይደርሱም ክህደት ተብለው እንደሚጠሩ እንረዳለን።
እዚህ ሐዲሥ ውስጥ ክህደት በማለት የሚፈለገው በአህሉ ሱናዎች ባጠቃላይ ስምምነት መሰረት ከእስልምና የማያስወጣውን ትንሹን ክህደት ነው። ምክንያቱም አላህ አማኞች በሚጋደሉበትና በሚጋጩበት ወቅት እንኳ ለነርሱ የእምነት ወንድማማችነትን አፅድቋልና። አላህ እንዲህ ብሏል {ከምእመናንም የሆኑ ሁለት ጭፍሮች ቢጋደሉ በመካከላቸው አስታርቁ} ከሚለው {ምእመናኖች ወንድማማቾች ናቸው።} [አል‐ሑጁራት: 9 ‐10] እስከሚለው ድረስ ይህን ያስረዳናል።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

