አላህ የትንሳኤ ቀን የመጀመሪያዎቹንም የመጨረሻዎቹንም የሰበሰበ ጊዜ የሁሉም ከዳተኛ አርማው (ባንዲራው) ከፍ ይደረጋል። "ይህ እከሌ የእከሌ ልጅ የፈፀመው ከዳተኝነቱ ነው።" ይባላልም።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከኢብኑ ዑመር ረዺየሏሁ ዐንሁማ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ብለዋል: "አላህ የትንሳኤ ቀን የመጀመሪያዎቹንም የመጨረሻዎቹንም የሰበሰበ ጊዜ የሁሉም ከዳተኛ አርማው (ባንዲራው) ከፍ ይደረጋል። "ይህ እከሌ የእከሌ ልጅ የፈፀመው ከዳተኝነቱ ነው።" ይባላልም።»
Explanation
Benefits
በደሙ ወይም በክብሩ ወይም በምስጢሩ ወይም በገንዘቡ አምኖህ ላንተ የሰጠውን እምነት መክዳት ይህ ሁሉ የተዛተበት ክዳት ውስጥ ይካተታል።
ቁርጡቢይ እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ ለዐረቦች መነገሩ ተመሳሳዩን ይሰሩት የነበረው ድርጊት ስለነበር ነው። እነርሱ ቃሉን ለሚሞላ ነጭ ባንዲራ ይተክሉለት ነበር። ለከዳተኛ ደግሞ እርሱን ለማውገዝና ለመውቀስ ጥቁር ባንዲራ ይተክሉ ነበር። ሐዲሡም ለከዳተኛ ተመሳሳይ ነገር እንደሚደረግ አስፈረደ። ይህም የትንሳኤ ቀን ባህሪው ታውቆ የትንሳኤ ቀን የቆሙ ሰዎች እንዲያወግዙት ነው።"
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «ይህ ሐዲሥ የትንሳኤ ቀን ሰዎች በአባቶቻቸው እንደሚጠሩ ማሳያ ነው። ይህም ሐዲሡ ውስጥ "ይህ እከሌ የእከሌ ልጅ የፈፀመው ከዳተኝነት ነው።" ይባላል ስላሉ ነው።»
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

