የጀነት ሰዎች ጀነት የገቡ ጊዜ አላህ ተባረከ ወተዓላ እንዲህ ይላል "አንዳች ነገር እንድጨምርላችሁ ትፈልጋላችሁን?
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከሱሀይብ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል: «የጀነት ሰዎች ጀነት የገቡ ጊዜ አላህ ተባረከ ወተዓላ እንዲህ ይላል "አንዳች ነገር እንድጨምርላችሁ ትፈልጋላችሁን?" እነርሱም "ፊታችንን አላበራህልንምን? ጀነት አስገብተህስ ከእሳት አላዳንከንምን?" ይላሉ። ነቢዩ እንዲህ አሉ "የፊቱን ግርዶሽ ይገልጣል። ወደ ጌታቸው ዐዘ ወጀል ከመመልከት የበለጠ ተወዳጅ የሆነ አንዳችም ነገር አልተሰጣቸውም።"»
Explanation
እንድጨምርላችሁ የምትፈልጉት አንዳች ነገር አለን?
ሁሉም የጀነት ሰዎችም እንዲህ ይላሉ: ፊታችንን አላበራኸውምን? ጀነት አስገብተህስ ከእሳት አላዳንከንምን?
አላህም ግርዶሹን አስወግዶ ይገልጠዋል። የፊቱ ግርዶሽም ብርሃን ነው። ወደ ጌታቸው ዐዘ ወጀል ከመመልከት የበለጠ ተወዳጅ ነገርም አይሰጣቸውም።
Benefits
ከጀነት ፀጋዎች ትልቁ ፀጋ አማኞች ጌታቸውን መመልከታቸው ነው።
የጀነት ሰዎች ሁሉ ደረጃቸው የተለያየ ቢሆን እንኳ ጌታቸውን ይመለከታሉ።
አላህ አማኞችን ጀነት በማስገባት ችሮታውን እንደሚውል እንረዳለን።
በመልካም ተግባርና አላህንና መልክተኛውን (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በመታዘዝ ወደ ጀነት መቻኮል አንገብጋቢ እንደሆነ እንረዳለን።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

