ከናንተ ምርጡ እኔ ያለሁበት (ዘመን) ትውልድ ነው። ከዚያም ከነርሱ በኋላ ቀጥለው የሚመጡት፤ ከዚያም ከነርሱ ቀጥለው የሚመጡት ናቸው።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከዒምራን ቢን ሑሰይን (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ ብለዋል: "ከናንተ ምርጡ እኔ ያለሁበት (ዘመን) ትውልድ ነው። ከዚያም ከነርሱ በኋላ ቀጥለው የሚመጡት፤ ከዚያም ከነርሱ ቀጥለው የሚመጡት ናቸው።" ዒምራንም እንዲህ አለ: "ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ከሳቸው ትውልድ በኋላ ሁለት ትውልዶችን ይጥቀሱ ወይም ሶስት አላውቅም።" ከዚያም ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ አሉ: "የሚከዱ የማይታመኑ፤ ምስክርነት ሳይጠየቁ የሚመሰክሩ፤ ስለትን ተስለው ስለታቸውን የማይሞሉ፤ በነርሱ ላይ ደንዳና ሰውነት የሚስተዋልባቸው ሰዎች ከናንተ በኋላ ይመጣሉ።"»
Explanation
Benefits
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ ሶሐቦች ከታቢዒዮች የበለጡ መሆናቸውን፤ ታቢዒዮች ደግሞ ከአትባዑ ታቢዒን የበለጡ መሆናቸውን ያስይዛል። ነገር ግን ይህ በላጭነት እንደ ጥቅል ነው ወይስ በተናጠልም ጭምር ነው? የሚለው ጥያቄ ጥናት የሚፈልግ ጉዳይ ነው። አብዛኛዎቹ ዑለማ ግን ሁለተኛውን አቋም መርጠዋል።"
የሶስቱን የመጀመርያ ትውልዶች መንገድ አጥብቆ በመከተል ላይ መጠቆሙን ያስረዳናል። ዘመኑ ለነቢያዊው ዘመን የቀረበ በሆነ ቁጥር በደረጃና በእውቀት የበለጠ ለመሆን እንዲሁም የነቢዩን (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) መመሪያ ለመከተል የተገባ ነውና።
ስለት ማለት: አንድ ለአቅመ አዳም የደረሰና አይምሮው ጤነኛ የሆነ ሰው ግዴታነትን በሚጠቁም ማንኛውም ንግግር አላህ ግዴታ ያላደረገበትን አንድን አምልኮ ራሱ ላይ ግዴታ ማድረጉ ነው።
ከዳተኝነት፣ ስለትን አለመሙላትና ቀልብን በዱንያ ማንጠልጠል መወገዙን እንረዳለን።
ባለመብቱ ምስክር ሊሆነው እንደሚችል እያወቀም ምስክርነት ሳይጠይቀው መመስከር መወገዙን እንረዳለን። ባለመብቱ እርሱ ምስክር እንደሆነ ካላወቀው ግን "ምርጡን ምስክር አልነግራችሁምን? ሳይጠየቅ በፊት ለመመስከር የሚመጣ ምስክር ነው።" የሚለው የነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ንግግር ውስጥ የሚካተት ነው።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

