እኔ የማትጎዳና የማትጠቅም ድንጋይ መሆንህን አውቃለሁ። እኔ ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ሲስሙህ ባላይህ ኖሮ አልስምህም ነበር።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከዑመር (ረዺየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራውን ይውደድለትና - እንደተላለፈው: "ዑመር ወደ ጥቁሩ ድንጋይ (ሐጀሩል አስወድ) መጣና ሳመው። እንዲህም አለ: እኔ የማትጎዳና የማትጠቅም ድንጋይ መሆንህን አውቃለሁ። እኔ ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ሲስሙህ ባላይህ ኖሮ አልስምህም ነበር።"
Explanation
Benefits
ጥቁሩን ድንጋይ በመሳም የሚፈለገው የአላህን መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና መከተል ነው።
ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "ሀሳቡም ይህ ድንጋይ መጥቀምም ሆነ መጉዳትን አይችልም ነው። እንደማንኛውም እንደማይጎዱና እንደማይጠቅሙ ፍጡራን እርሱም የተፈጠረ ድንጋይ ነው። ዑመር ይህንን ንግግር በዚህ መድረክ ያሰራጨውም በሁሉም ሀገር ምስክር እንዲሆንና ከተለያዩ ሀገራት የተገኙ የሐጅ ሰዎች እንዲሸመድዱት ነው።"
አምልኮ የተገደበ ነው። አላህና መልክተኛው ከደነገጉት ውጪ አይደነገግም።
ጥበቡ ባይታወቅ እንኳ አምልኮዋ ትክክለኛ ከሆነች ትሰራለች። ሰዎች ትእዛዙን ተግባራዊ ማድረጋቸውና መታዘዛቸው ራሱ ከአምልኮ ዋነኛ ጥበቦች መካከል አንዱ ነውና።
እንደ ድንጋይና ከርሱ ውጪ ያሉ መሰል ነገሮችን በሸሪዓ እስካልታዘዘ ድረስ በአምልኳዊ መንገድ እነርሱን መሳም መከልከሉን እንረዳለን።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

