HadeethEnc · 1.23.0
ከናንተ መካከል ሰውነቱን ጤነኛ ሆኖ፤ በነፍሱና በቤተሰቡ ላይ ደህና ሆኖ፤ የእለት ቀለቡ እርሱ ዘንድ ኑሮ ያነጋ ሰው ዱንያን በሙሉ እንደተረከባት ይቁጠር።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከዐብደላህ ቢን ሚሕሰን አልአንሷሪይ (ረዺየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ አሉ: "ከናንተ መካከል ሰውነቱን ጤነኛ ሆኖ፤ በነፍሱና በቤተሰቡ ላይ ደህና ሆኖ፤ የእለት ቀለቡ እርሱ ዘንድ ኑሮ ያነጋ ሰው ዱንያን በሙሉ እንደተረከባት ይቁጠር።"
02
Explanation
ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከናንተ ከሙስሊሞች መካከል ሰውነቱን ከበሽታና ህመም ጤነኛና ደህና ሆኖ፤ በነፍሱ፣ በቤተሰቡ፣ በዘመዶቹና በመንገዱ ላይ ሁሉ ሳይፈራ ደህንነቱ የተጠበቀለት ሆኖ፤ እርሱ ዘንድ በቂ ሐላል የሆነ የቀን ቀለብ ኑሮት ያነጋ ሰው ዱንያ ባጠቃላይ ለርሱ እንደተሰበሰበችለት አምሳያ መሆኑን ተናገሩ።
03
Benefits
የሰው ልጅ ጤንነት፣ ደህንነትና ቀለብ የግድ እንደሚያስፈልገው መገለፁን እንረዳለን።
አንድ ባሪያ በነዚህ ፀጋዎች አላህን ማመስገንና ማወደስ እንደሚገባው እንረዳለን።
ከዱንያ ቸልተኛ በመሆንና በመብቃቃት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
አንድ ባሪያ በነዚህ ፀጋዎች አላህን ማመስገንና ማወደስ እንደሚገባው እንረዳለን።
ከዱንያ ቸልተኛ በመሆንና በመብቃቃት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
Attribution
[ቲርሚዚና ኢብኑማጀህ ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

