HadeethEnc · 1.23.0
ለይለቱል ቀድርን በረመዷን የመጨረሻ አስር ቀናቶች በጎደሎ ቁጥሮቹ ውስጥ ፈልጓት።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከዓኢሻ - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ ብለዋል: "ለይለቱል ቀድርን በረመዷን የመጨረሻ አስር ቀናቶች በጎደሎ ቁጥሮቹ ውስጥ ፈልጓት።"
02
Explanation
ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ለይለቱል ቀድርን ለመፈለግ መልካም ስራዎችን በማብዛት መታገል እንደሚገባ አነሳሱ። ለይለቱል ቀድርም በሁሉም ዓመት ከረመዷን የመጨረሻዎቹ አስር ቀናት በጎዶሎው ምሽቶች መሆኗ ተስፋ ይደረጋል። እነርሱም: ሀያ አንደኛ፣ ሀያ ሶስተኛ፣ ሀያ አምስተኛ፣ ሀያ ሰባተኛና ሀያ ዘጠነኛ ሌሊቶች ናቸው።
03
Benefits
የለይለቱል ቀድርን ትሩፋትና እርሷን በመፈለግ ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
ከአላህ ጥበብና እዝነት መካከል ሰዎች እርሷን ፍለጋ በአምልኮ ሲታገሉ ምንዳቸው እንዲጨምር ይህቺን ሌሊት መደበቁ ነው።
ለይለቱል ቀድር በረመዷን የመጨረሻዎቹ አስር ቀናት ውስጥ ነው። በጎዶሎዎቹ ቀናት መሆኑም ይበልጥ ተስፋ ይደረጋል።
ለይለቱል ቀድር ማለት ከረመዷን የመጨረሻዎቹ አስር ሌሊቶች መካከል አንዷ ናት። እርሷም አላህ ዐዘ ወጀል በነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ላይ ቁርአን ያወረደበት ሌሊት ናት። ይህችንም ሌሊት በበረከትና በደረጃዋ ታላቅነት ከአንድ ሺህ ወር የተሻለች አድርጓታል። ስለዚህም በዚህች ሌሊት መልካም ስራ መስራት ታላቅ ስፍራ ያለው ነው።
(ለይለቱል ቀድር) ተብላ የተጠራቸው ወይ ልቅና ከሚለው ቃል ተወስዶ ነው። (እከሌ ቀድሩ ታላቅ ነው።) ማለትም ልቅናው ከፍ ያለ ነው ማለት ነው። ልክ እንደዚሁ ቀድሯ ትልቅ የሆነችው ሌሊት ሲባል "ቀድር" የሚለው ቃል ሌሊት ለሚለው ቃል ገላጭ ይሆናል። ማለትም የላቀችዋ (የተከበረችዋ) ሌሊት ማለት ነው። ማለትም ደረጃዋ፣ ልቅናዋና ስፍራዋ የላቀ ማለት ነው። {እኛ (ቁርአንን) በተባረከው ምሽት አወረድነው።} [አድዱኻን:3] ወይም ደሞ (ተቅዲር) መወሰኛ ከሚለው ቃል ነው የተወሰደችው ቢባልም ያስኬዳል። ማለትም በዚህች ምሽት ውስጥ በአመት ውስጥ የሚከሰተው ነገር ይወሰናል። {በውስጧ የተወሰነው ነገር ሁሉ ይልለያል።} [አድዱኻን:4]
ከአላህ ጥበብና እዝነት መካከል ሰዎች እርሷን ፍለጋ በአምልኮ ሲታገሉ ምንዳቸው እንዲጨምር ይህቺን ሌሊት መደበቁ ነው።
ለይለቱል ቀድር በረመዷን የመጨረሻዎቹ አስር ቀናት ውስጥ ነው። በጎዶሎዎቹ ቀናት መሆኑም ይበልጥ ተስፋ ይደረጋል።
ለይለቱል ቀድር ማለት ከረመዷን የመጨረሻዎቹ አስር ሌሊቶች መካከል አንዷ ናት። እርሷም አላህ ዐዘ ወጀል በነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ላይ ቁርአን ያወረደበት ሌሊት ናት። ይህችንም ሌሊት በበረከትና በደረጃዋ ታላቅነት ከአንድ ሺህ ወር የተሻለች አድርጓታል። ስለዚህም በዚህች ሌሊት መልካም ስራ መስራት ታላቅ ስፍራ ያለው ነው።
(ለይለቱል ቀድር) ተብላ የተጠራቸው ወይ ልቅና ከሚለው ቃል ተወስዶ ነው። (እከሌ ቀድሩ ታላቅ ነው።) ማለትም ልቅናው ከፍ ያለ ነው ማለት ነው። ልክ እንደዚሁ ቀድሯ ትልቅ የሆነችው ሌሊት ሲባል "ቀድር" የሚለው ቃል ሌሊት ለሚለው ቃል ገላጭ ይሆናል። ማለትም የላቀችዋ (የተከበረችዋ) ሌሊት ማለት ነው። ማለትም ደረጃዋ፣ ልቅናዋና ስፍራዋ የላቀ ማለት ነው። {እኛ (ቁርአንን) በተባረከው ምሽት አወረድነው።} [አድዱኻን:3] ወይም ደሞ (ተቅዲር) መወሰኛ ከሚለው ቃል ነው የተወሰደችው ቢባልም ያስኬዳል። ማለትም በዚህች ምሽት ውስጥ በአመት ውስጥ የሚከሰተው ነገር ይወሰናል። {በውስጧ የተወሰነው ነገር ሁሉ ይልለያል።} [አድዱኻን:4]
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

