HadeethEnc · 1.23.0
ወላሂ አላመነም! ወላሂ አላመነም! ወላሂ አላመነም!" "የአላህ መልክተኛ ሆይ ማን ነው?" ተባሉ። እርሳቸውም "ጎረቤቱ ተንኮሉን ያላመነው ሰው ነው።" አሉ።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአቡ ሹረይሕ (ረዲየላሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ አሉ፦ «"ወላሂ አላመነም! ወላሂ አላመነም! ወላሂ አላመነም!" "የአላህ መልክተኛ ሆይ ማን ነው?" ተባሉ። እርሳቸውም "ጎረቤቱ ተንኮሉን ያላመነው ሰው ነው።" አሉ።»
02
Explanation
ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ማሉ። መሃላቸውንም ሶስት ጊዜ አድርገው አፅንዖት ሰጥተው እንዲህ አሉ: "ወላሂ አላመነም! ወላሂ አላመነም! ወላሂ አላመነም!" አሉ። ሶሐቦችም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ማን ነው ያላመነው?" አሉ። እርሳቸውም "ከክዳቱ፣ ከግፉና ከክፋቱ አንፃር ጎረቤቱ የሚፈራው ነው።" አሉ።
03
Benefits
ጎረቤቱ ከግፉና ከክፋቱ የማያምኑት ሰው ላይ ኢማን ውድቅ መደረጉ ትልቅ ወንጀል መሆኑንና ኢማኑ የጎደለው መሆኑን ይጠቁማል።
ለጎረቤት መልካምን በመዋል ላይና ጎረቤትን በንግግር ወይም በተግባር ማወክን በመተው ላይ ጠንካራ የሆነ ማነሳሳት መደረጉን እንረዳለን።
ለጎረቤት መልካምን በመዋል ላይና ጎረቤትን በንግግር ወይም በተግባር ማወክን በመተው ላይ ጠንካራ የሆነ ማነሳሳት መደረጉን እንረዳለን።
Attribution
[ቡኻሪ ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

