HadeethEnc · 1.23.0
አቡ ዘር ሆይ! መረቅ የቀቀልክ ጊዜ ውሃውን አብዛ! ጎረቤቶችህንም ተከታተል።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአቡ ዘር ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል: "አቡ ዘር ሆይ! መረቅ የቀቀልክ ጊዜ ውሃውን አብዛ! ጎረቤቶችህንም ተከታተል።"»
02
Explanation
ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- አቡ ዘር አልጚፋሪይን ረዺየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - መረቅ የቀቀለ ጊዜ ውሃውንና መረቁን እንዲያበዛና ከመረቁ ለጎረቤቶቹ በመላክም እንዲከታተላቸው አነሳሱት።
03
Benefits
ከጎረቤት ጋር መልካም በሆነ መልኩ በመኗኗር ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
በጎረቤቶች መካከል ስጦታ መሰጣጠታቸው እንደሚወደድ እንረዳለን። ይህም ውዴታን ስለሚያመጣና ቅርርብን ስለሚጨምር ነው። ምግቡ የሚጣራ መአዛ ካለውና ጎረቤቶቹም እንደሚያስፈልጋቸው ከታወቀ ደግሞ ይህን ስጦታ መስጠት አፅንዖት የተሰጠው ጉዳይ ይሆናል።
ብታንስ እንኳ የገራልንን ጥሩን ነገር በመለገስ ላይና ለሙስሊሞች ደስታ ምክንያት በመሆን ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
በጎረቤቶች መካከል ስጦታ መሰጣጠታቸው እንደሚወደድ እንረዳለን። ይህም ውዴታን ስለሚያመጣና ቅርርብን ስለሚጨምር ነው። ምግቡ የሚጣራ መአዛ ካለውና ጎረቤቶቹም እንደሚያስፈልጋቸው ከታወቀ ደግሞ ይህን ስጦታ መስጠት አፅንዖት የተሰጠው ጉዳይ ይሆናል።
ብታንስ እንኳ የገራልንን ጥሩን ነገር በመለገስ ላይና ለሙስሊሞች ደስታ ምክንያት በመሆን ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
Attribution
[ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

