(ላኢላሃ ኢለሏህ ወሕደሁ ላሸሪከ ለህ ለሁልሙልኩ ወለሁልሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር) የሚለውን ውዳሴ በቀን ውስጥ መቶ ጊዜ ያለ ሰው
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ብለዋል: "(ላኢላሃ ኢለሏህ ወሕደሁ ላሸሪከ ለህ ለሁልሙልኩ ወለሁልሐምዱ ወሁወ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር) የሚለውን ውዳሴ በቀን ውስጥ መቶ ጊዜ ያለ ሰው ለርሱ አስር ባሪያዎችን ነፃ እንዳወጣ ይቆጠርለታል፤ መቶ ምንዳም ለርሱ ይጻፍለታል፤ መቶ ኃጢአቶችም ከርሱ ላይ ይሰረዛሉ፤ ቀኑንም እስኪያመሽ ድረስም ለርሱ ከሸይጧን መጠበቂያ ትሆንለታለች፤ እርሱ ከሰራው የበለጠ አብዝቶ የሰራ ሰው ካልሆነ በቀር አንድም ሰው ከርሱ የበለጠም አልሰራም።" ትርጉሙም (ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ የለም። ብቸኛና አጋር የሌለውም ነው። ንግስና የርሱ ነው። ምስጋናም ለርሱ ነው። እርሱም በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው።)
Explanation
ማንም በላጭ ስራ ይዞ አይመጣም።
Benefits
የበላይ የሆነው አላህ በባሮቹ ላይ ያለው ችሮታ ሰፊ መሆኑን እንረዳለን። ይህም ለእያንዳንዱ ሰው ገር የሆነን ዚክር (ውዳሴ) መደንገጉና በዛም ላይ ትልቅን ምንዳ በማስቀመጡ ነው።
ይህንን ዚክር በቀን ውስጥ ከመቶ ጊዜ በላይ ቢል ሐዲሡ ውስጥ የተጠቀሰውን መቶ ጊዜ ያለ ሰው የሚያገኘውን ምንዳም ያገኛል በጨመረው ልክም ሌላ ምንዳ ይኖረዋል። ይህም ከተባለው በላይ መጨመሩ ምንም ደረጃ የለውም ወይም ያበላሸዋል ተብሎ መጠኑን መተላለፉ የተከለከለው የቁጥር ገደብ ውስጥ የሚገባ አይደለም።
ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "የሐዲሡ ጥቅል መልዕክት በግልፅ የሚያስረዳን ይህንን ሐዲሡ ውስጥ የተጠቀሰውን ምንዳ በቀን ውስጥ አከታትሎም ይበል ወይም በተለያዩ ስፍራዎች ከፋፍሎም ይበል ወይም የተወሰነውን የቀኑ መጀመሪያ ላይ የተወሰነውን ደግሞ የቀኑ መጨረሻ ላይ ይበል ውዳሴውን መቶ ጊዜ በማለቱ ብቻ ያገኘዋል። ነገር ግን አጠቃላይ ቀኑን ከሸይጧን መጠበቂያ እንዲሆንለት የቀኑ መጀመሪያ ላይ ቢለው በላጭ ነው።"
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

