የአላህ ፊት የሚፈለግበትን እውቀት የዱንያን ጥቅም ለማግኘት ካልሆነ በቀር ለሌላ ግብ የማይማረው ከሆነ የትንሳኤ ቀን የጀነትን ሽታ አያገኝም።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ ረዲየላሁ ዐንሁ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል፦ «የአላህ መልዕክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ብለዋል፡ "የአላህ ፊት የሚፈለግበትን እውቀት የዱንያን ጥቅም ለማግኘት ካልሆነ በቀር ለሌላ ግብ የማይማረው ከሆነ የትንሳኤ ቀን የጀነትን ሽታ አያገኝም።"»
Explanation
Benefits
ሸሪዓዊ እውቀትን ለይዩልኝ ወይም ለዱንያ ጥቅም በመገልገል ዙሪያ ከባድ ማስጠንቀቂያ መምጣቱንና ይህም ከትላልቅ ወንጀል የሚመደብ መሆኑን እንረዳለን።
ለአላህ ብሎ እውቀትን የፈለገ ሰውና ያንን ተከትሎ ዱንያ ብትመጣለት እርሷን መጠቀም ይፈቀድለታልም ምንም አይጎዳውምም።
ሲንዲይ እንዲህ ብለዋል: "ሐዲሡ ውስጥ "የጀነት ሽታን አያገኝም" መባሉ። ለርሱ ጀነት እርም መሆኗን ለማጋነን ነው። የአንድን ነገር ሽታዋንም የማያገኝ ሰው በርሷ ተጠቃሚነቱም የማይታሰብ ነው።"
የአላህ ፊት የሚፈለግበትን እውቀት ስራ ለመቀጠሪያነት ወይም ለሌላ አላማ ብሎ የተማረ ሰው ከዚህ ወንጀሉ ወደ አላህ መመለስ አለበት። አላህ በተበላሸ ኒያው የተገኘውን ወንጀል ያብስለታል። እርሱ ጥራት ይገባውና የታላቅ ችሮታ ባለቤት ነው።
ይህ ሸሪዓዊ እውቀትን ለሚቀስም ሰው ማስጠንቀቂያ ነው። እንደምህንድስና፣ ኬምስትሪና ሌሎችንም የዱንያ እውቀቶች ለዱንያ ብሎ የተማረ ግን በኒያው ያሰበውን ያገኛል።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

