ስስታም ማለት እርሱ ዘንድ ተወስቼ በኔ ላይ ሶላት ያላወረደ ነው።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከሑሰይን ቢን ዐሊይ ቢን አቢጧሊብ (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል: "ስስታም ማለት እርሱ ዘንድ ተወስቼ በኔ ላይ ሶላት ያላወረደ ነው።"»
Explanation
የመጀመሪያው: ሶለዋት በማውረዱ ምክንያት ትንሽም ይሁን ብዙ የማይከስርበት፣ ገንዘብ የማያወጣበት፣ ጉልበቱን የማያፈስበት በሆነ ነገር ላይ መሰሰት ስለሆነ፤
ሁለተኛው: በአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ላይ ሶለዋት ባለማውረዱ በርሳቸው ላይ ሶላት የማውረድን ምንዳ በነፍሱ ላይ ስለሳሳና ስለነፈጋት ነው። በርሳቸው ላይ ሶለዋት ባለማውረዱ ትእዛዝን ለመተግበርና ምንዳን ለማግኘት ሊፈፅመው ግዴታ የሆነበትን ሐቅ ከመፈፀም ታቅቧልም ሰስቷልም።
ሶስተኛው: በርሳቸው ላይ ሶለዋት ማውረድ የተወሰነውን የነቢዩን (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ሐቅ መወጣት ነው። ያስተማሩን፣ ያቀኑን፣ ወደ አላህ ተባረከ ወተዓላ የጠሩን፣ ይህንን ወሕይና ሸሪዓ ይዘው የመጡልን እርሳቸው ናቸው። ከአላህ ተባረከ ወተዓላ በኋላ የመመራታችን ምክንያት እርሳቸው ናቸው። በርሳቸው ላይ ሶለዋት ያላወረደ ሰው በርግጥም በነፍሱ ላይም ስስታም ሆኗል። ለነቢዩም (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ካላቸው ሐቆች መካከል በትንሹ ሐቅ እንኳ ስስታም ሆኗል።
Benefits
በማንኛውም ወቅት በነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ላይ ሶለዋት ማውረድ በላጭ ከሆኑ አምልኮዎችና መቃረቢያዎች መካከል ነው። እርሳቸው በሚወሱበት ወቅት ደሞ በላጭነቱ ጠንከር ይላል።
ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: «በነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ላይ ሶለዋት ሲያወርድ ሶለዋትና ሰላምን ሰብስቦ ይበል። በአንዱ ላይ ብቻ አይቆጠብ። (ሶለላሁ ዐለይሂ) ብቻ ወይም (ዐለይሂ ሰላም) ብቻ አይበል።»
{አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ ሶላትን ያወርዳሉ።} በሚለው የአላህ ቃል ዙሪያ አቡል ዐሊያህ እንዲህ ብለዋል: «አላህ በነቢዩ ላይ ሶለዋት አወረደ ማለት እርሳቸውን ማወደሱ ነው። ሶለዋት ከመላእክትና ከሰው ሲሆን ደግሞ ዱዓእ ነው።»
ሐሊሚይ እንዲህ ብለዋል: (አላሁመ ሶሊ ዐላ ሙሐመድ) የሚለው ትርጉም አላህ ሆይ! በዱንያ መወሳታቸውን ከፍ በማድረግ፣ ሃይማኖታቸውን የበላይ በማድረግ፣ ሸሪዓቸውን ዘውታሪ በማድረግ አላቃቸው። በመጪው አለም ደግሞ ለኡመታቸው አማላጅ በማድረግ፣ ምንዳቸውንና አጅራቸውን በማተለቅ፣ ለመጀመሪያውም ሆነ ለመጨረሻው ፍጡር በምስጉኑ ስፍራ ደረጃቸውን በመግለፅ፣ አላህ ፊት ምስክር ከሆኑ ቅርቦች ባጠቃላይ በማስቀደም አላቃቸው ማለት ነው።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

