ከባህር ውሃ ጋር ብትቀላቀል የባህሩን ውሃ የምታበላሽ የሆነችን ንግግር ተናገርሽ።" አሏት።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከአማኞች እናት ዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው እንዲህ አለች: «ለነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ለሰፊያ (ነውር’ኮ) እንዲህ እንዲህ ነገሯ ራሱ ይበቃሃል። አልኳቸው። (አንዱ የሐዲሥ ዘጋቢ እንዲህ እንዲህ ነገሯ ይበቃሃል በማለት የፈለገችው እጥረቷን ነው ብለዋል።) እርሳቸውም "ከባህር ውሃ ጋር ብትቀላቀል የባህሩን ውሃ የምታበላሽ የሆነችን ንግግር ተናገርሽ።" አሏት። "እንዲህም አለች "ለርሳቸው የሆነ ሰው የሚያደርገውን አስመስዬ በድርጊት አሳየኃቸው።" እርሳቸውም "ለኔ እንዲህ እንዲህ ቢሰጠኝ እንኳ ሰውን ማስመሰል አያስደስተኝም (አልወድም)።" አሉ።»
Explanation
Benefits
በማሳነስና ዝቅ በማድረግ መልኩ ሰዎችን ማስመሰልና የነርሱን ሁኔታ መከተል ከተከለከለው ሀሜት ይመደባል።
አካላዊ ነውሮችን መግለፅ የሀሜት አንድ ክፍል ነው።
ቃዲ እንዲህ ብለዋል: «"መዝጅ" ማለት ሌላን ነገር ወደርሱ መቀላቀል፣ መለወጥ ማለት ነው። ሀሳቡም ይህ ሀሜት ባህር ውስጥ የሚቀላቀል ቢሆን ኖሮ የባህሩ ውሃ ከመብዛቱም ጋር ውሃውን ይለውጠው ነበር ማለት ነው። ጥቂት ተግባራት ቢቀላቀልበትስ ምን ሊሆን ይችል?»
በሚስቶች መካከል የሚከሰት ቅናት መጠቀሱን እንመለከታለን።
ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ውግዝ ተግባርን አለማፅደቃቸው።
ዱንያና ውስጧ ያሉ ነገሮች ከአላህ ውዴታና ከአላህ አለመቆጣት ጋር ሲነፃፀሩ ያነሱ መሆናቸውን እንረዳለን።
እስልምና ክብሮች በንግግርም ሆነ በተግባር እንዳይደፈሩ በመከልከል ክብር እንዲጠበቅ ያዘዘ የመልካም ስነምግባር ሃይማኖት ነው። ምክንያቱም ክብርን መንካት በሙስሊሞች መካከል ጠላትነትንና ጥላቻን የሚፈጥር ነውና።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

