'አንተ አለቃችን የሆንክ!' አልን። እርሳቸውም 'የሁሉም አለቃው አላህ ነው።' አሉ። እኛም 'በደረጃ በላጫችን እጅግ ታላቅ የሆንክ!' አልን። እርሳቸውም 'የምትሉትን በሉ ወይም ከምትሉት ከፊሉን በሉ ሰይጣን (ወደ ወሰን ማለፍ እንዳይጎትታቹ) አይጫወትባችሁ' አሉ።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከዐብደላህ ቢን ሺኺር (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ፦ «ከበኒ ዓሚር ልዑካን ጋር ወደ አላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሄድኩ። 'አንተ አለቃችን የሆንክ!' አልን። እርሳቸውም 'የሁሉም አለቃው አላህ ነው።' አሉ። እኛም 'በደረጃ በላጫችን እጅግ ታላቅ የሆንክ!' አልን። እርሳቸውም 'የምትሉትን በሉ ወይም ከምትሉት ከፊሉን በሉ ሰይጣን (ወደ ወሰን ማለፍ እንዳይጎትታቹ) አይጫወትባችሁ' አሉ።»
Explanation
Benefits
በንግግር ወሰን ማለፍ መከልከሉንና በአነጋገር ሚዛናዊ መሆን እንደሚገባ እንረዳለን።
ተውሒድ ከሚያጎድፉት ንግግሮችም ሆነ ተግባራት ጥበቃ እንደተደረገለት እንረዳለን።
በማወደስ ወሰን ከማለፍ መከልከሉን እንረዳለን። ይህም ከሰይጣን መግቢያዎች አንዱ ነው።
በሐዲሱ የተጠቀሰው ንግግራቸው ለመተናነስ ያህልና ሰዎቹ በርሳቸው ላይ ወሰን እንዳያልፉ ስለፈሩ እንጂ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የአደም ዘር አለቃ ናቸው።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

