HadeethEnc · 1.23.0
ወደ ቅናቻ የተጣራ ሰው የተከተሉትን ሰዎች አምሳያ ምንዳ ያገኛል። ይህም (ለርሱ የሚሰጠው ምንዳ) ከምንዳቸው አንዳች ሳይቀነስ ነው።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል፦ "ወደ ቅናቻ የተጣራ ሰው የተከተሉትን ሰዎች አምሳያ ምንዳ ያገኛል። ይህም (ለርሱ የሚሰጠው ምንዳ) ከምንዳቸው አንዳች ሳይቀነስ ነው። ወደ ጥመት የተጣራ ሰውም የተከተሉትን ሰዎች አምሳያ ወንጀል ይኖርበታል። ይህም (በርሱ ላይ የሚኖረው ወንጀል) ከወንጀሎቻቸው ምንም ሳይቀነስ ነው።"
02
Explanation
በንግግሩ ወይም በተግባሩ እውነትና መልካም ወዳለበት መንገድ ሰዎችን የመራ፣ የጠቆመና የቀሰቀሰ ሰው የተከታዩን አምሳያ ምንዳ እንደሚያገኝና ይህም ከተከታዩ ምንዳ አንዳችም ሳይቀነስ እንደሆነ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ገለፁ። በንግግር ወይም በተግባር ወንጀልና ኃጢአት ወይም የማይፈቀድ ነገር ወዳለበት የጥመትና የክፋት መንገድ ሰዎችን የጠቆመ ሰውም የተከታዩን አምሳያ ወንጀልና ኃጢአት ይኖርበታል። ይህም ከነርሱ ወንጀል አንዳችም ሳይቀነስ ነው።
03
Benefits
በትንሹም ሆነ በብዛት ወደ ቅናቻ መጣራት ያለውን ደረጃ እንረዳለን። ተጣሪ ሰው በርሱ ጥሪ የሰሩ ሰዎችን ምንዳ አምሳያ ይኖረዋል። ይህም የአላህን ትልቅ ችሮታና ሙሉ ቸርነት ያስረዳናል።
በትንሹም ሆነ በብዛት ወደ ጥመት የመጣራትን አደጋ እንረዳለን። ወደ ጥመት የሚጣራም ሰው በሰበካው የሰራን ሰው ወንጀል አምሳያ በርሱ ላይ ይኖርበታል።
ምንዳ የሚሰጠው በስራው አይነት እንደሆነ እንረዳለን። ወደ መልካም የተጣራ ሰው በጥሪው የሰራን ሰው ምንዳ አምሳያ ለርሱ ይኖረዋል። ወደ መጥፎ የሰበከ ሰውም በሰበካው የሰራን ሰው ወንጀል አምሳያ በርሱ ላይ ይኖርበታል።
አንድ ሙስሊም ወንጀልን ግልፅ በማድረጉ ሰዎች አይተው እንዳይከተሉት መጠንቀቅ አለበት። በዚህ ላይ ሆን ብሎ ባይቀሰቅስ እንኳ በተከተሉት ሰዎች ልክ ወንጀል ላይ ይወድቃልና።
በትንሹም ሆነ በብዛት ወደ ጥመት የመጣራትን አደጋ እንረዳለን። ወደ ጥመት የሚጣራም ሰው በሰበካው የሰራን ሰው ወንጀል አምሳያ በርሱ ላይ ይኖርበታል።
ምንዳ የሚሰጠው በስራው አይነት እንደሆነ እንረዳለን። ወደ መልካም የተጣራ ሰው በጥሪው የሰራን ሰው ምንዳ አምሳያ ለርሱ ይኖረዋል። ወደ መጥፎ የሰበከ ሰውም በሰበካው የሰራን ሰው ወንጀል አምሳያ በርሱ ላይ ይኖርበታል።
አንድ ሙስሊም ወንጀልን ግልፅ በማድረጉ ሰዎች አይተው እንዳይከተሉት መጠንቀቅ አለበት። በዚህ ላይ ሆን ብሎ ባይቀሰቅስ እንኳ በተከተሉት ሰዎች ልክ ወንጀል ላይ ይወድቃልና።
Attribution
[ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

