HadeethEnc · 1.23.0
አንዳችሁ ከኢማም በፊት ጭንቅላቱን ቀና ያደረገ ጊዜ አላህ ጭንቅላቱን የአህያ ጭንቅላት እንዳያደርገው ወይም አላህ የሰውነት ቅርፁን የአህያ የሰውነት ቅርፅ እንዳያደርግበት አይፈራምን?!
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል፦ "አንዳችሁ ከኢማም በፊት ጭንቅላቱን ቀና ያደረገ ጊዜ አላህ ጭንቅላቱን የአህያ ጭንቅላት እንዳያደርገው ወይም አላህ የሰውነት ቅርፁን የአህያ የሰውነት ቅርፅ እንዳያደርግበት አይፈራምን?!"
02
Explanation
ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ጭንቅላቱን ከኢማሙ በፊት ቀና የሚያደርግ ሰው አላህ ጭንቅላቱን የአህያ ጭንቅላት ሊያደርግበት ወይም የሰውነት ቅርፁን የአህያ ቅርፅ ሊያደርግበት እንደሚችል በመግለፅ ከባድ ዛቻን አስተላለፉ።
03
Benefits
አንድ ተከታይ ከኢማሙ ጋር ያለው የመከተል ሁኔታ አራት ነው። ከአራቱ ሶስቱ የተከለከሉ ናቸው። እነርሱም: መቅደም፣ እኩል መፈፀምና ኋላ መቅረት ናቸው። ለተከታይ የተደነገገው ኢማሙን መከተል ነው።
ተከታይ የሆነ ሰው ሶላት ውስጥ ኢማሙን መከተል ግዴታው እንደሆነ እንረዳለን።
ከኢማሙ በፊት ራሱን ቀና የሚያደርግ ሰው ላይ የሰውነት ቅርፁ ወደ አህያ ቅርፅ እንደሚለወጥ የመጣው ዛቻ ሊሆን የሚችል ነገር ነው። ይህም ወደ ሌላ ፍጥረት ከመለወጥ የሚመደብ ነው።
ተከታይ የሆነ ሰው ሶላት ውስጥ ኢማሙን መከተል ግዴታው እንደሆነ እንረዳለን።
ከኢማሙ በፊት ራሱን ቀና የሚያደርግ ሰው ላይ የሰውነት ቅርፁ ወደ አህያ ቅርፅ እንደሚለወጥ የመጣው ዛቻ ሊሆን የሚችል ነገር ነው። ይህም ወደ ሌላ ፍጥረት ከመለወጥ የሚመደብ ነው።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

