ሱብሓነላህ! ሙእሚን'ኮ ነጃሳ አይሆንም።" አሉት።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: «ከመዲና መንገዶች በአንዱ መንገድ ላይ እርሱ ጀናባ ላይ ሆኖ ሳለ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሲያገኙት ከእይታቸው ተደብቆ በመሄድ ገላውን ታጠበ። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) ፈልገው አጡት። በሚመጣበት ወቅትም "አቡ ሁረይራ ሆይ! የት ነበርክ?" አሉት። እርሱም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! እኔን ያገኙኝ ጀናባ ላይ ሆኜ ስለነበር ገላዬን ሳልታጠብ ከርሶ ጋር መቀማመጥን ጠላሁ።" አላቸው። የአላህ መልክተኛም (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) "ሱብሓነላህ! ሙእሚን'ኮ ነጃሳ አይሆንም።" አሉት።»
Explanation
Benefits
አማኝ የሆነ ሰው በህይወትም ሆነ ሞቶ ንፁህ ነው።
የክብር፣ የእውቀትና የመልካምነት ባለቤቶችን ማላቅና ባማረ ሁኔታ ላይ ሁነን ከነርሱ ጋር መቀማመጥ እንደሚገባ እንረዳለን።
ተከታይ የሆነ ሰው የሚከተለውን አካል አስፈቅዶ መሄዱ የተደነገገ እንደሆነ እንረዳለን። ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) አቡ ሁረይራን (አላህ መልካም ስራውን ይውደድለትና) እርሳቸው ሳያውቁ በመሄዱ አውግዘውታል። ይህም አስፈቅዶ መሄድ ካማሩ ስነ-ስርዓቶች መካከል አንዱ ስለሆነ ነው።
በመደነቅ ወቅት ሱብሓነሏህ (ጥርት ለአላህ የተገባ ነው) ማለት እንደሚገባ እንረዳለን።
አንድ ሰው የሚያሳፍር የሆነን ነገር አስፈላጊ ሲሆን መናገሩ እንደሚፈቀድ እንረዳለን።
ከሃዲ ነጃስ ነው። ነገር ግን ነጃሳነቱ እምነተ ብልሹ ስለሆነ በመሆኑ ሕዋሳዊ (ውስጣዊ) ነው።
ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "በተጨማሪ ከዚህ ሐዲሥ ከምንወስዳቸው ቁምነገሮች መካከል: ከመልካም ስነስርዓት መካከል አንድ ዓሊም ተከታዩ ስህተት ላይ ወድቋል ብሎ የፈራውን ነገር ሲመለከት ጠይቆት ትክክሉን በመንገር ብይኑን ማብራራት እንዳለበት ነው። አላህ ነው አዋቂው።"
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

