የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- መጀመሪያ ወሕይ ወደርሳቸው መውረድ የጀመረው በእንቅልፋቸው የሚያዩት መልካም ህልም ነበር።
ከአማኞች እናት ዓኢሻ ረዲየሏሁ ዐንሃ - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው እንዲህ አለች: «የአላህ መልክተኛ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- መጀመሪያ ወሕይ ወደርሳቸው መውረድ የጀመረው በእንቅልፋቸው የሚያዩት መልካም ህልም ነበር። ንጋት ብርሃን (እንደተፍለቅላቂ ጎህ) በገሃዱ አለም የሚከሰት ቢሆን እንጂ አንድም ህልም አያዩም ነበር። ከዚያም ከሰዎች መገለል እርሳቸ…

