ምላስህ አላህን በማውሳት ከመርጠብ አይወገድ።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከዐብደላህ ቢን ቡስር - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «አንድ ሰውዬ ወደ ነቢዩ በመምጣት እንዲህ አለ: "የአላህ መልክተኛ ሆይ! የእስልምና ድንጋጌዎች በርግጥም በኛ ላይ በዙብን። አጥብቄ የምይዘውን ዋናውን በር ይንገሩን።" እርሳቸውም እንዲህ አሉ: "ምላስህ አላህን በማውሳት ከመርጠብ አይወገድ።"» በሌላ ዘገባ: በሙዓዝ ቢን ጀበል - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ሐዲሥ እንደተላለፈው: ሙዓዝ እንዲህ አሉ: «"የአላህን መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- የተለያየሁት የመጨረሻ ንግግሬ "ወደ አላህ እጅግ የሚያቃርበኝና መልካሙ ስራ ማንኛው ስራ ነው?" የሚል ነበር። እርሳቸውም: "ምላስህ አላህን ዓዘ ወጀል በማውሳት እርጥብ ሆኖ መሞትህ ነው።" በማለት መለሱልኝ።»
Explanation
ነቢዩም (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በሁሉም ሁኔታና ወቅት ምላሱ በ"ተስቢሕ" (ሱብሐነሏህ)፣ በ"ተሕሚድ" (አልሐምዱሊላህ)፣ ምህረት በመጠየቅ (አስተጝፊሩሏህ)፣ ዱዓ በማድረግና በመሳሰሉት አላህን በማውሳት ዘውትሮ ምላሱን ማንቀሳቀስና ማርጠብ እንዳለበት ጠቆሙት።
Benefits
ከአላህ ችሮታ መካከል ትልቁ ምንዳን ማግኛ መንገዶችን ማቅለሉ ተጠቃሽ ነው።
ባሮች በበጎና መልካም እጣ ፈንታቸው እንደሚበላለጡ እንረዳለን።
እንደ "ሱብሐነላህ"፣ "አልሐምዱሊላህ"፣ "ላኢላሃ ኢለላህ"፣ "አላሁ አክበር"ና ከዚህም ውጪ ያሉ አዝካሮችን ከቀልብ ጋር በማስተሳሰር በምላስ አላህን አብዝቶ ማውሳት የብዙ ግዴታ ያልሆኑ (ሱና) አምልኮዎችን ደረጃ ይይዛል።
ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ለሁሉም ጠያቂዎች የሚስማማቸውን መልስ እየጠበቁ መመለሳቸውን እንረዳለን።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

