HadeethEnc · 1.23.0
አላህ ግዴታዎችን ደነግጓል። (ባለመስራት) አታጥፏት። ድንበሮችን ወስኗል። አትተላለፏት። ነገሮችን ከልክሏል አትዳፈሯት። ለናንተው በማዘን ሳይረሳው አንዳንድ ነገሮችንም ዝም ብሏል፤ ስለርሷ አትፈላፈሉ።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአቡ ሠዕለባ አልኹሸኒይ ጁርሡም ቢን ናሺር -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል: "አላህ ግዴታዎችን ደነግጓል። (ባለመስራት) አታጥፏት። ድንበሮችን ወስኗል። አትተላለፏት። ነገሮችን ከልክሏል አትዳፈሯት። ለናንተው በማዘን ሳይረሳው አንዳንድ ነገሮችንም ዝም ብሏል፤ ስለርሷ አትፈላፈሉ።"
02
Explanation
ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ በማለት ተናገሩ። አላህ ብዙ ነገሮችን ግዴታ አድርጓልም ደንግጓልም። አጥብቃችሁ ያዙት፤ በመተው ወይም በመዘናጋት እንዳታጓድሉት። አላህ እናንተን የሚያቅቡና እርሱ ከማይወደው የሚያግዷችሁን የተወሰኑ ማቀቢያዎችንና ማገጃዎችን አድርጓልና በሸሪዓ ካዘዘው አትለፉ። አላህ ውግዝ ነገሮችን ስለከለከለ አትፈፅሟትም አትቅረቧትም። ከነዚህ ውጪ ያሉን ግን ለባሮቹ በማዘን ትቷቸዋል ዝምም ብሏቸዋል። ልክ በመሰረቱ እንደነበረው ፍቁድ እንደሆነ ይቀራል። ስለርሱም አትፈላፈሉ።
03
Benefits
ይህ ሐዲሥ አላህ ብቻ ህግ ደንጋጊ እንደሆነና ነገሮች በእጁ እንደሆኑ ይጠቁማል።
ይህ ሐዲሥ በመፍረድም ይሁን በመፍቀድ ረገድ የሸሪዓን መርሆዎች ያካተተ ሐዲሥ ነው። ምክንያቱም ሸሪዓዊ ብይን: ወይ ዝም የተባለ ነው ወይም የተዘረዘረ ነው። የተዘረዘረ የሸሪዓ ብይን ወይ በግዴታነትም ይሁን በተወዳጅነት የታዘዘ ነው፤ ወይም በእርምነት (ክልክልነት) ደረጃም ይሁን በውግዝነት የተከለከለ ነው፤ ወይም ደሞ የተፈቀደ ነው።
አላህ ግዴታ ሳያደርገው፣ ገደብ ሳያበጅለት፣ ሳይከለክለው በዝምታ ያለፈው ነገር ፍቁድ ነው።
ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- በዚህ ግልፅና ፍንትው ባለ መልኩ ሐዲሡን መዘርዘራቸው ውብ የሆነ የማብራራት ብቃት እንዳላቸው ያስረዳናል።
አላህ ግዴታ ያደረጋቸውን ነገሮች መጠባበቅ ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።
የአላህን ድንበሮች መተላለፍ ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
ይህ ሐዲሥ በመፍረድም ይሁን በመፍቀድ ረገድ የሸሪዓን መርሆዎች ያካተተ ሐዲሥ ነው። ምክንያቱም ሸሪዓዊ ብይን: ወይ ዝም የተባለ ነው ወይም የተዘረዘረ ነው። የተዘረዘረ የሸሪዓ ብይን ወይ በግዴታነትም ይሁን በተወዳጅነት የታዘዘ ነው፤ ወይም በእርምነት (ክልክልነት) ደረጃም ይሁን በውግዝነት የተከለከለ ነው፤ ወይም ደሞ የተፈቀደ ነው።
አላህ ግዴታ ሳያደርገው፣ ገደብ ሳያበጅለት፣ ሳይከለክለው በዝምታ ያለፈው ነገር ፍቁድ ነው።
ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- በዚህ ግልፅና ፍንትው ባለ መልኩ ሐዲሡን መዘርዘራቸው ውብ የሆነ የማብራራት ብቃት እንዳላቸው ያስረዳናል።
አላህ ግዴታ ያደረጋቸውን ነገሮች መጠባበቅ ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።
የአላህን ድንበሮች መተላለፍ ክልክል መሆኑን እንረዳለን።
Attribution
[رواه الدارقطني في سننه وغيره]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

