ከናንተ መካከል በርሱና በአላህ መካከል አስተርጓሚ ሳይኖር አላህ የሚያናግረው ቢሆን እንጂ አንድም ሰው የለም
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከዓዲይ ቢን ሓቲም (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል: "ከናንተ መካከል በርሱና በአላህ መካከል አስተርጓሚ ሳይኖር አላህ የሚያናግረው ቢሆን እንጂ አንድም ሰው የለም ወደ ቀኝ ይመለከታል። ያሳለፈውን እንጂ ሌላ ምንም አይመለከትም። ወደ ግራም ይመለከታል ካሳለፈው በቀር ሌላ ምንም አይመለከትም። ከፊትለፊቱ ይመለከታል በፊትለፊቱ ከእሳት ውጭ ሌላ ምንም አይመለከትም። በተምር ክፋይ እንኳ ቢሆን እሳትን ተጠንቀቁ።"»
Explanation
Benefits
የፍርዱ ቀን አላህ ወደ ባሮቹ በመካከላቸው ግርዶሽ፣ አማካኝና አስተርጓሚ ሳይኖር የሚቀርብ መሆኑን እንረዳለን። ስለዚህም የትኛውም አማኝ የጌታውን ትእዛዝ ከመቃረን መጠንቀቅ ይገባዋል።
አንድ ሰው የሚመፀውተው ነገር ትንሽ እንኳ ብትሆን ከእሳት መጠበቂያው ልትሆን ስለምትችል ሊያሳንሳት እንደማይገባው እንረዳለን።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

