HadeethEnc · 1.23.0
በዚህ መስጂዴ የሚሰገድ ሶላት ከርሱ ውጪ ከሚሰገዱ አንድ ሺህ ሶላቶች የተሻለ ነው። የተከበረው መስጊድ (መስጂደል ሐራም) ሲቀር።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው : ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ብለዋል: "በዚህ መስጂዴ የሚሰገድ ሶላት ከርሱ ውጪ ከሚሰገዱ አንድ ሺህ ሶላቶች የተሻለ ነው። የተከበረው መስጊድ (መስጂደል ሐራም) ሲቀር።"
02
Explanation
ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በርሳቸው መስጂድ የሚሰገድ ሶላትን ደረጃ ገለፁ። እርሱም መካ ውስጥ ከሚገኘው ከተከበረው መስጂድ ውጪ ምድር ላይ በሚገኙ መስጂዶች ከሚሰገድ ሶላት ሁሉ በአንድ ሺህ እጥፍ ይበልጣል። በተከበረው መስጂድ (መስጂደል ሐራም) የሚሰገድ ሶላት ግን በርሳቸው መስጂድ ከሚሰገድ ሶላትም ይበልጣል።
03
Benefits
በተከበረው መስጂድና በነቢዩ መስጂድ የሚሰገድ ሶላት ምንዳ እጥፍ ድርብ መሆኑን እንረዳለን።
በተከበረው መስጊድ የሚሰገድ ሶላት ከርሱ ውጪ በሚገኙ መስጂዶች ከሚሰገዱ ሶላቶች በመቶ ሺህ በላጭ ነው።
በተከበረው መስጊድ የሚሰገድ ሶላት ከርሱ ውጪ በሚገኙ መስጂዶች ከሚሰገዱ ሶላቶች በመቶ ሺህ በላጭ ነው።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

