HadeethEnc · 1.23.0
አላህ ዘንድ እጅግ ተወዳጁ ስፍራ መስጂዶች ናቸው። አላህ ዘንድ እጅግ የሚጠላው ስፍራ ገበያዎች ናቸው።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል፦ "አላህ ዘንድ እጅግ ተወዳጁ ስፍራ መስጂዶች ናቸው። አላህ ዘንድ እጅግ የሚጠላው ስፍራ ገበያዎች ናቸው።"
02
Explanation
ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- አላህ ዘንድ እጅግ ተወዳጁ ስፍራ መስጂዶች እንደሆኑ ተናገሩ። ይኸውም የአምልኮ ቤቶችና ምስረታቸውም አላህን በመፍራት ላይ ስለሆነ ነው። አላህ ዘንድ እጅግ የተጠላውም ስፍራ ገበያዎች እንደሆኑ ተናገሩ። ይኸውም በአብዛኛው ማታለል፣ መሸወድ፣ ወለድ፣ የውሸት መሃላ፣ ቃልን ማፍረስና አላህን ከማስታወስ ችላ የሚባልበት ስፍራ ስለሆነ ነው።
03
Benefits
የመስጂዶች ክብርና ደረጃን እንረዳለን። ይህም የአላህ ስም በብዛት የሚወሳባቸው ስለሆኑ ነው።
የአላህን ውዴታ በመፈለግ መስጂዶችን አዘውትሮ በመያዝ ላይ፣ ወደ መስጂድ አብዝቶ በመመላለስ ላይና ወደ ገበያዎች ደግሞ አስፈላጊ ካልሆነ በቀር በአላህ ወደመጠላት የሚያደርሱ ሰበቦች ላይ ከመውደቅ ለመራቅ ሲባል አብዝቶ ባለመመላለስ ላይ መነሳሳቱን እንመለከታለን።
ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "መስጂዶች የአላህ እዝነት የሚወርድባቸው ስፍራዎች ሲሆኑ ገበያዎች ደግሞ ከዚህ ተቃራኒ ናቸው።"
የአላህን ውዴታ በመፈለግ መስጂዶችን አዘውትሮ በመያዝ ላይ፣ ወደ መስጂድ አብዝቶ በመመላለስ ላይና ወደ ገበያዎች ደግሞ አስፈላጊ ካልሆነ በቀር በአላህ ወደመጠላት የሚያደርሱ ሰበቦች ላይ ከመውደቅ ለመራቅ ሲባል አብዝቶ ባለመመላለስ ላይ መነሳሳቱን እንመለከታለን።
ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "መስጂዶች የአላህ እዝነት የሚወርድባቸው ስፍራዎች ሲሆኑ ገበያዎች ደግሞ ከዚህ ተቃራኒ ናቸው።"
Attribution
[ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

