ፀሀይ በመግቢያዋ እስክትወጣ ድረስ ሰዓቲቱ አትቆምም። ከመግቢያዋ የወጣችና ሰዎች የተመለከቷት ጊዜ ሁሉም ያምናሉ
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦ "ፀሀይ በመግቢያዋ እስክትወጣ ድረስ ሰዓቲቱ አትቆምም። ከመግቢያዋ የወጣችና ሰዎች የተመለከቷት ጊዜ ሁሉም ያምናሉ። ይህም {ከዚህ በፊት አማኝ ያልሆነችን ነፍስ እምነትዋ ወይም በእምነትዋ (ጊዜ) በጎ ያልሠራችን (ነፍስ ጸጸትዋ) አይጠቅማትም።} [አል አንዓም: 158] የተባለበት ወቅት ነው። ሰዓቲቱ ሁለት ሰዎች ሊገበያዩ ልብሶቻቸውን ዘርግተው ሳይገበያዩም ሳይሰበስቡትምም (ድንገት) ትከሰታለች፤ ሰዓቲቱ ሰውዬው ያለበውን ወተት (ለመጠጣት) እንደዞረ ሳይጠጣው (ድንገት) ትከሰታለች፤ ሰዓቲቱ ሰውዬው ምንጩን እያስተካከለ ከሱ ሳይጠጣ (ድንገት) ትከሰታለች፤ ሰዓቲቱ አንዳችሁ ጉርሻውን ወደ አፉ አስጠግቶ ሳይበላት (ድንገት) ትከሰታለች።"
Explanation
Benefits
ለሰዓቲቱ በኢማንና መልካም ሥራ መዘጋጀት እንደሚገባ መነሳሳቱ ምክንያቱም ሰዓቲቱ በድንገት ስለምትከሰት።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

