አላህ አንድን ባሪያ የወደደው ጊዜ ጂብሪልን ይጠራውና እንዲህ ይለዋል: "እኔ እከሌን እወደዋለሁና ውደደው።" ጂብሪልም ይወደዋል።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል: «አላህ አንድን ባሪያ የወደደው ጊዜ ጂብሪልን ይጠራውና እንዲህ ይለዋል: "እኔ እከሌን እወደዋለሁና ውደደው።" ጂብሪልም ይወደዋል። ቀጥሎ ጂብሪል ሰማይ ውስጥ እንዲህ በማለት ይጣራል: "አላህ እከሌን ይወደዋልና ውደዱት።" የሰማይ ነዋሪዎችም ይወዱታል። ከዚያም ምድር ላይ ተቀባይነት ይኖረዋል። አላህ አንድን ባሪያ የጠላ ጊዜም ጂብሪልን በመጥራት እንዲህ ይለዋል: "እኔ እከሌን እጠላዋለሁና ጥላው።" ጂብሪልም ይጠላዋል። ቀጥሎም ጂብሪል ለሰማይ ነዋሪዎች እንዲህ በማለት ይጣራል: "አላህ እከሌን ይጠላዋልና ጥሉት።" እነርሱም ይጠሉታል። ከዚያም ምድር ላይ ተጠይነትን ይኖርበታል።»
Explanation
Benefits
አላህ የወደደውን ሰው የሰማይና የምድር ነዋሪዎችም ይወዱታል። አላህ የጠላው ሰውም የሰማይና የምድር ነዋሪዎችም ይጠሉታል።
ሲንዲይ እንዲህ ብለዋል: (ምድር ላይ ተቀባይነት ይኖረዋል) የሚለው የግድ ሁሉም ዘንድ ተወዳጅነትን አይጠቁምም። ይልቁንም አላህ በምድር ላይ እንዲኖረው የሻለትን ያህል ቅቡልነት ነው የሚኖረው። ክፉዎችች ለመልካሞች ያላቸው ጠላትነት እየታወቀ እንዴት አጠቃላይ ውዴታ ይኖረዋል?!
የተለያዩ አይነቶችን መልካም ስራዎች ግዴታም ይሁን ሱና አሟልቶ በመስራት ላይ መነሳሳቱንና ወንጀሎችና ቢድዓዎች የአላህን ቁጣ የሚያመጡ ስለሆኑ መጠንቀቅ እንደሚገባ እንረዳለን።
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: "ከዚህ ሐዲሥ ከምንወስዳቸው አስተምህሮቶች መካከል በሰዎች ቀልብ መወደድ በአላህ የመወደድ ምልክት ነው። ይህንንም የጀናዛ ምዕራፍ ውስጥ "እናንተ በምድር የአላህ ምስክር ናችሁ።" በሚል የተዘገበው ሐዲሥ ያጠናክረዋል።"
ኢብኑል ዐረቢ አልማሊኪይ እንዲህ ብለዋል: "የምድር ነዋሪዎች ሲባል የሚፈለገው ሰውዬውን የሚያውቁት ማለት ነው እንጂ የማያውቁትና ስለርሱ ሰምተው የማያውቁትም ይወዱታል ማለት አይደለም።"
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

