አልሏሁምመ ኢንኒ አዑዙ ቢከ ሚነልዐጅዚ ወልከሰሊ ወልጁብኒ ወልቡኽሊ ወልሀረሚ ወዐዛቢል ቀብር ፤ አልሏሁምመ አቲ ነፍሲ ተቅዋሃ ወዘክኪሃ አንተ ኸይሩ መን ዘክካሃ፤ አንተ ወሊይዩሃ ወመውላሃ፤ አልሏሁምመ ኢንኒ አዑዙ ቢከ ሚን ዒልሚን ላ የንፈዑ፤ ወሚን ቀልቢን ላ የኽሸዑ፤ ወሚን ነፍሲን ላ ተሽበዑ፤ ወሚን ደዕወቲን ላ ዩስተጃቡ ለሃ።" (ትርጉሙም፡ "አላህ ሆይ! እኔ ከስንፍና ፣ ከመታከት ፣ ከፈሪነት ፣ ከስስት ፣ ከመጃጀትና ከቀብር ቅጣት ባንተ እጠበቃለሁ። አላህ ሆይ! ለነፍሴ ፍራቻዋን ስጣት፤ ነፍሴን ለማጥራት የተሻልከው አንተው ነህና ነፍሴን አጥራት፤ አንተ ረዳቷና ተቆጣጣሪዋ ነህና። አላህ ሆይ! እኔ ከማይጠቅም ዕውቀት፣ አንተን ከማይፈራ ልብ፣ ከማትጠግብ ነፍስ፣ ተቀባይነት ከሌላት ዱዓም ባንተ እጠበቃለሁ።")
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከዘይድ ቢን አርቀም - አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «እኔ የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ይሉ ከነበሩት ውጪ አልልም። እርሳቸው እንዲህ ይሉ ነበር: "አልሏሁምመ ኢንኒ አዑዙ ቢከ ሚነልዐጅዚ ወልከሰሊ ወልጁብኒ ወልቡኽሊ ወልሀረሚ ወዐዛቢል ቀብር ፤ አልሏሁምመ አቲ ነፍሲ ተቅዋሃ ወዘክኪሃ አንተ ኸይሩ መን ዘክካሃ፤ አንተ ወሊይዩሃ ወመውላሃ፤ አልሏሁምመ ኢንኒ አዑዙ ቢከ ሚን ዒልሚን ላ የንፈዑ፤ ወሚን ቀልቢን ላ የኽሸዑ፤ ወሚን ነፍሲን ላ ተሽበዑ፤ ወሚን ደዕወቲን ላ ዩስተጃቡ ለሃ።" (ትርጉሙም፡ "አላህ ሆይ! እኔ ከስንፍና ፣ ከመታከት ፣ ከፈሪነት ፣ ከስስት ፣ ከመጃጀትና ከቀብር ቅጣት ባንተ እጠበቃለሁ። አላህ ሆይ! ለነፍሴ ፍራቻዋን ስጣት፤ ነፍሴን ለማጥራት የተሻልከው አንተው ነህና ነፍሴን አጥራት፤ አንተ ረዳቷና ተቆጣጣሪዋ ነህና። አላህ ሆይ! እኔ ከማይጠቅም ዕውቀት፣ አንተን ከማይፈራ ልብ፣ ከማትጠግብ ነፍስ፣ ተቀባይነት ከሌላት ዱዓም ባንተ እጠበቃለሁ።")
Explanation
Benefits
አላህን በመፍራትና እውቀትን በማሰራጨትና በእውቀት በመስራት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን።
ጠቃሚ እውቀት ማለት ነፍስን የሚያጠራ የአላህን ፍራቻ ነፍስ ውስጥ የሚፈጥርና ከነፍሱ ተነስታ ወደ ሁሉም አካላቶቹ የሚሄድን የአላህ ፍራቻ የሚያስገኝ ነው።
የሚተናነስ ልብ ማለት የሚፈራ፣ የአላህ ስም ሲወሳ የምትርበተበት ከዚያም የምትረጋጋና የምትለዝብ ቀልብ ናት።
ለዱንያ መጓጓትና ከስሜቶቿና ከጥፍጥናዋ አለመጥገብ መወገዙን እንረዳለን። ስለዚህም ለዱንያ ጥቅም እጅግ የምትጓጓና የምትስገበገብ ነፍስ ለሰውየው የጠላቶች ጠላት ናት። ስለዚህም ነው የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ከርሷ የተጠበቁት።
ሰውዬው ዱዓን ተመላሽ ከሚያደርጉና ተቀባይነትን ከሚያሳጡ ምክንያቶች ሊርቅ ይገባዋል።
ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥና ይህን የመሰሉ ቤት የሚመቱ ዱዓዎች ዑለሞች ለተናገሩት ማስረጃ ነው። እርሱም: ዱዓን ቤት በሚመቱ ንግግሮች ማድረግ የተወገዘው ያለ አቅሙ ቃላት ለመምረጥ ሲጥር ነው። ቃላት መረጣ መተናነስን፣ መዋደቅንና ስራን ለአላህ ማጥራትን ያስወግዳል። ከመዋደቅ፣ ፈላጊነትን ከማሳየትና በባዶ ልብ ዱዓ ከማድረግ ያዘናጋል። ነገር ግን ያለመጣጣር፣ የተሟላ አንደበተ ርቱዕ ለመሆን አይምሮን ሳያስጨንቁና የመሳሰሉትን ሳያደርጉ ወይም በሐዲሥ ውስጥ ተጠቅሶ የተሸመደደን ቤት የሚመታ ዱዓ ማለት ችግር የለውም። እንደውም የተሻለ ነው።"
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

