ሰዎች የትንሳኤ ቀን ባዶ እግራቸውን፣ ራቁትና ያልተገረዙ ሆነው ይሰበሰባሉ።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከአማኞች እናት ዓኢሻህ -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና- እንደተላለፈው እንዲህ ብላለች: «የአላህ መልክተኛን -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ፦ "ሰዎች የትንሳኤ ቀን ባዶ እግራቸውን፣ ራቁትና ያልተገረዙ ሆነው ይሰበሰባሉ።" እኔም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ወንዶችም ሴቶችም ባጠቃላይ ከፊሉ ወደ ከፊሉ እየተመለከተ?" አልኳቸው። ነቢዩም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - "ዓኢሻህ ሆይ! ጉዳዩኮ ከፊሉ ወደ ከፊሉ ከመመልከትም በላይ በጣም ከባድ ነው።" አሉኝ።»
Explanation
Benefits
ይህ ሐዲሥ የሰው ልጅ ካልተዘናጋ በቀር ወንጀል ላይ እንደማይወድቅ ያጠናክርልናል። የሰው ልጅ ያመፀውን ጌታ ታላቅነት ወይም የቅጣቱን ከባድነት ቢያስታውስ ኖሮ ለቅፅበት ያህል እንኳ እርሱን ከማውሳት፣ ከማመስገንና አሳምሮ ከማምለክ አይዘናጋም ነበር። ስለዚህም ነው የትንሳኤ ቀን የሚሰበሰቡ ሰዎች በነፍሳቸው ከመጠመዳቸው የተነሳ ከፊሉ ወደ ከፊሉ የማይመለከት ሆኖ ታየዋለህ።
በአላህ መልክተኛ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ዘመን የነበሩ ሴቶች የነበራቸው ሃፍረት ከፍተኛ እንደሆነ እንረዳለን። ይኸውም ዓኢሻ -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና- ወንዱም ይሁን ሴቱ ፍጥረታት ባጠቃላይ ራቁታቸውን እንደሚቀሰቀሱ ስትሰማ ሃፍረት በተሞላበት መልኩ ማብራሪያ ከመጠየቋ የምንረዳው ነው።
ሲንዲይ እንዲህ ብለዋል: "ሁሉም ስለራሱ ጉዳይ የተጠመደ በመሆኑ ስለ ወንድሙ ሁኔታ ምንም አያውቅም። ታላቁ አላህ እንዲህ ብሏል: {ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ሁኔታ አለው።} [ዐበሰ: 37] አንድም ሰው ወደ ሌላው ሃፍረተ ገላ ሊመለከት እንኳ አይዞርም።"
ግርዛት: ለወንድ ልጅ: ክርክሩን የሸፈነውን ቆዳ መቁረጥ ሲሆን ለሴት ደግሞ: ከብልት መግቢያ ቀዳዳ ከፍ ብሎ ያለውን የአውራ ዶሮ ቆብ የሚመስለውን ቆዳ መቁረጥ ነው።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

