መሪያችሁን ስሙ ታዘዙም! በነርሱ ላይ የተሸከሙት ግዴታ አለባቸው። በናንተም ላይ የተሸከማችሁት ግዴታ አለባችሁ።" አሉ።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከዋኢል አልሐድረሚይ እንደተላለፈው እንዲህ አለ: «ሰለማ ቢን የዚድ አልጁዕፊይ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና የአላህን መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ በማለት ጠየቀ: "የአላህ ነቢይ ሆይ! ሐቃቸውን የሚጠይቁ ሐቃችንን ደግሞ የሚከለክሉን መሪዎች በኛ መካከል ቢመጡ ምን ያዙናል እስኪ ንገሩን?" እርሳቸውም ከርሱ ዘወር አሉ። እርሱም ድጋሚ ጠየቃቸው እርሳቸው ግን አሁንም ከርሱ ዘወር አሉ። እርሱም በድጋሚ ለሁለተኛ ወይም ለሶስተኛ ጊዜ ጠየቃቸው። በዚህ ጊዜ አሽዐሥ ቢን ቀይስ ጎተተው። እርሳቸውም "መሪያችሁን ስሙ ታዘዙም! በነርሱ ላይ የተሸከሙት ግዴታ አለባቸው። በናንተም ላይ የተሸከማችሁት ግዴታ አለባችሁ።" አሉ።»
Explanation
ነቢዩም ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ይህንን ጥያቄ እንደጠሉ በሚያሳብቅ መልኩ ከርሱ ዘወር አሉ። ጠያቂው ግን ለሁለተኛና ለሶስተኛ ጊዜ ጥያቄውን ደገመላቸው። አሽዐሥ ቢን ቀይስም (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራውን ይውደድለትና - ጠያቂውን ዝም ለማስባል ጎተተው።
ነቢዩም (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ሲመልሱለት እንዲህ አሉ: "የመሪዎቻችሁን ንግግር ስሙ፤ ትእዛዛቸውን ታዘዙ። በነርሱም ላይ የተጣለባቸው ፍትህን የማስፈን፣ የህዝብን ሐቅ የማሟላት ኃላፊነት አለባቸው። በናንተም ላይ የተጣለባችሁ የመታዘዝ፣ ሐቃቸውን የመወጣት፣ በሚያደርሱት ግፍ ላይ የመታገስ ግዴታ አለባችሁ።
Benefits
መሪዎች ካለባቸው ግዴታ በማጓደላቸው ሰዎችም በተመሳሳይ ያለባቸውን ግዴታ እንዲያጓድሉ ብቁ አያደርግም። ሁሉም ስለስራው ተጠያቂ፤ ባጓደለውም የሚያዝ ነው።
ሃይማኖት በመለዋወጥ ላይ የተገነባ አይደለም። ነገር ግን ልክ እዚህ ሐዲሥ ውስጥ እንደመጣው ሌላኛው በተቃራኒ ያለበትን ግዴታ ቢያጓድል ራሱ እኛ ግን ግዴታ የሆነብንን መወጣት ነው።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

