የሰው ልጅ እንደሆዱ መጥፎን ቋት አልሞላም። የአደም ልጅ ወገቡን ቀና የሚያደርጉለት ጥቂት ጉርሻዎች ይበቁታል። (መጥገቡ) የማይቀር ከሆነ (የሆዱን) ሲሶውን ለምግቡ፣ ሲሶውን ለመጠጡ፣ ሲሶውን ለትንፋሹ ያድርግ።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከሚቅዳም ቢን መዕዲከሪበ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አለ: «የአላህ መልዕክተኛ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ: "የሰው ልጅ እንደሆዱ መጥፎን ቋት አልሞላም። የአደም ልጅ ወገቡን ቀና የሚያደርጉለት ጥቂት ጉርሻዎች ይበቁታል። (መጥገቡ) የማይቀር ከሆነ (የሆዱን) ሲሶውን ለምግቡ፣ ሲሶውን ለመጠጡ፣ ሲሶውን ለትንፋሹ ያድርግ።"
Explanation
Benefits
የመመገብ ኣላማው ጤንነትንና ሀይልን መጠበቅ ነው። ጤንነትና ሀይል ሲኖር ሰላማዊ ህይወት ይኖራል።
ሆድን በምግብ በመሙላት አካልም ላይ ሆነ ዲን ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች አሉ። ዑመር - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ ብለዋል: "ጠግቦ ከመብላት አደራችሁን ተጠንቀቁ። እጅግ ጠግቦ መብላት ሰውነትን የሚያበላሽና ከሶላትም የሚያሳንፍ ነው።"
አመጋገብ ከብይን አንፃር ሲታይ የተለያዩ ክፍሎች ይኖሩታል: ግዴታ የሆነ አመጋገብ: ይህም ህይወትን ለማቆየትና ባለመመገቡ ወደ ጉዳት የሚያደርስ ምግብ ነው። የሚፈቀድ የሆነ አመጋገብ: ይህም የግድ መብላት ካለበት መጠን የጨመረና ጉዳት ያደርሳል ተብሎ የማይሰጋ አመጋገብ ነው። የሚጠላ የሆነ አመጋገብ: ይህም ጉዳት ያደርሳል ተብሎ የሚያሰጋ ምግብ ነው። ክልክል የሆነ አመጋገብ: ይህም ጉዳት እንደሚያደርስ የታወቀ አመጋገብ ነው። የሚወደድ የሆነ አመጋገብ: ይህም አላህን በማምለክ ላይ ለመታገዝ ተብሎ የሚመገቡት አመጋገብ ነው። ይህንንም በሐዲሡ ውስጥ በሶስት ደረጃዎች ተጠቃለው እናገኛቸዋለን። የመጀመሪያው: ሆድን መሙላት ነው። ሁለተኛው: ጀርባውን የሚያቆምለት ያህል ጉርሻዎች ናቸው። ሶስተኛው: "ሲሶውን ለምግቡ፣ ሲሶውን ለመጠጡ፣ ሲሶውን ለትንፋሹ ያድርግ።" ያሉት ነው። ይህ ሁሉ ግን የሚመገበው ምግቡ ሐላል ከሆነ ነው።
ይህ ሐዲሥ ከህክምና መርሆዎች መካከል አንዱ መርህ ነው። የህክምና እውቀት የሚሽከረከረው በሶስት መሰረቶች ላይ ነው። ሀይልን መጠበቅ፣ ምግብን ማሳነስና አቅምን መጠቀም ላይ ነው። ይህ ሐዲሥ ሁለቱን የመጀመሪያዎቹን ጠቅሷቸዋል። አላህም እንዲህ ብሏል: {ብሉም ጠጡም አታባክኑም። እርሱ አባካኞችን አይወድምና።} [አልአዕራፍ: 31]
እስልምና የሰው ልጅ ለዲኑም ሆነ ለዱንያው የሚጠቅመውን ማካተቱ የዚህ ሸሪዓን ሙሉነት ያስረዳናል።
ሸሪዓ ካካተታቸው እውቀቶች መካከል የህክምና መሰረቶችና የህክምና አሰጣጥ አይነቶች አንዱ ነው። በሸሪዓ ስለማርና ጥቁር አዝሙድ የመጣውም ይህን ያመሳክርልናል።
የሸሪዓ ህግጋቶች ጥበብን ያጠቃለሉ መሆናቸውን እንረዳለን። የሸሪዓ ህግጋቶች ጉዳትን በመከላከልና ጥቅምን በማምጣት ላይ የተገነቡ ናቸው።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

