ምግብ ስትበሉ ተሰብሰቡ። (አንድ ላይ ብሉ) የአላህንም ስም በምግባቹ ላይ አውሱ። አላህ ምግባችሁን ይባርክላችኋል።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከወሕሺይ ቢን ሐርብ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው: «እነርሱ "የአላህ መልክተኛ ሆይ! እኛ እየበላን አንጠግብም።" አሏቸው። እርሳቸውም "ምናልባት ተበታትናችሁ ለየብቻ እየበላችሁ ይሆን?" ብለው ጠየቋቸው። እነርሱም "አዎን" አሉ። እርሳቸውም "ምግብ ስትበሉ ተሰብሰቡ። (አንድ ላይ ብሉ) የአላህንም ስም በምግባቹ ላይ አውሱ። አላህ ምግባችሁን ይባርክላችኋል።"»
Explanation
ነቢዩም - የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና - ለነርሱ እንዲህ አሏቸው: "ምን አልባት ስትበሉ ተበታትናችሁ ለየብቻ ነው እንዴ የምትበሉት?" እነርሱም: "አዎን" አሉ። እርሳቸውም: "ተሰብሰቡ ሳትበታተኑ ብሉ። ስትበሉ ቢስሚላህ በማለት የአላህን ስም አውሱ። በዛም ይባረክላችኋልም ትጠግባላችሁም።" አሏቸው።
Benefits
መበታተን ባጠቃላይ መጥፎ ሲሆን መሰባሰብ በጠቃላይ ደግሞ መልካም ነው።
በመሰባሰብ ላይና ሲበሉ ቢስሚላህ በማለት ላይ መነሳሳቱን እንመለከታለን።
ሲንዲይ እንዲህ ብለዋል: "በመሰባሰብ ቀለቦች ላይ በረከት ይወርዳል። የአላህን ስም በማውሳት ደግሞ የሸይጧንን ወደ ምግቡ መድረስ ያቅባል።"
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

