HadeethEnc · 1.23.0
እንዳልከው ከሆነ አንተ ትኩስ አመድ እያቃምካቸው ነው። በዚህ ሁኔታ ላይ እስከዘወተርክ ድረስም ከአላህ የሆነ አጋዥ ከአንተ ጋር አይወገድም።" አሉት።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው: «አንድ ሰውዬ እንዲህ አለ: "የአላህ መልክተኛ ሆይ! እኔ ቅርብ ዘመዶች አሉኝ። ዝምድናቸውን እቀጥላለሁ፤ እነርሱ ይቆርጡኛል። እኔ መልካም እውልላቸዋለሁ፤ እነርሱ መጥፎ ያደርጉብኛል። እኔ እታገሳቸዋለሁ፤ እነርሱ ግን ፀያፍ ተግባር ይፈፅሙብኛል።" እርሳቸውም "እንዳልከው ከሆነ አንተ ትኩስ አመድ እያቃምካቸው ነው። በዚህ ሁኔታ ላይ እስከዘወተርክ ድረስም ከአላህ የሆነ አጋዥ ከአንተ ጋር አይወገድም።" አሉት።»
02
Explanation
አንድ ሰውዬ ቅርብ ዘመዶች እንዳሉትና ከነርሱም ጋር በመልካም መስተጋብር እንደሚኗኗር እነርሱ ግን ከዚህ ተቃራኒ በሆነ መንገድ እንደሚኗኗሩት ለነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ስሞታ አቀረበ። እርሱ ይቀጥላቸዋልም፤ ይጠይቃቸዋልም፤ እነርሱ ግን ይቆርጡታል። በበጎነትና በታማኝነት ለነርሱ መልካም ቢውልም እነርሱ ግን በግፍና በድርቅና መጥፎ ይሰሩበታል። ይታገሳቸዋልም፤ ይቅር ይላቸዋልም፤ እነርሱ ግን በፀያፍ ንግግርና ተግባር ይቅርታውን ችላ ይላሉ። ከነዚህ ከተጠቀሱት ተግባራቸው ጋር ዝምድና መቀጠሌን ልግፋበትን?
ነቢዩም (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ለርሱ እንዲህ አሉት: እንዳወሳኸው ከሆነ አንተ ራሳቸውን እንዲያዋርዱና እንዲንቁ ነው ያደረግካቸው። በጎ መዋልህ በዝቶላቸው የነርሱ ነፍስ ግን ፀያፍ ተግባር ብቻ መስራቱ ልክ ትኩስ አመድ እንዳበላሀቸው ነው። አንተ ባወሳህልኝ በጎ መዋል ላይ እስከዘወተርክና እነርሱም ላንተ መጥፎ ማድረግ ላይ እስከዘወተሩ ድረስ በነርሱ ላይ የሚያግዝህና የነርሱን ማወክ የሚከላከልልህ ከአላህ ዘንድ የሆነ አጋዥም ከአንተ አይወገድም።
ነቢዩም (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ለርሱ እንዲህ አሉት: እንዳወሳኸው ከሆነ አንተ ራሳቸውን እንዲያዋርዱና እንዲንቁ ነው ያደረግካቸው። በጎ መዋልህ በዝቶላቸው የነርሱ ነፍስ ግን ፀያፍ ተግባር ብቻ መስራቱ ልክ ትኩስ አመድ እንዳበላሀቸው ነው። አንተ ባወሳህልኝ በጎ መዋል ላይ እስከዘወተርክና እነርሱም ላንተ መጥፎ ማድረግ ላይ እስከዘወተሩ ድረስ በነርሱ ላይ የሚያግዝህና የነርሱን ማወክ የሚከላከልልህ ከአላህ ዘንድ የሆነ አጋዥም ከአንተ አይወገድም።
03
Benefits
መጥፎ ስራን በጥሩ መመለስ መጥፎ አድራጊውን ወደ ትክክል ይመልሳል ተብሎ ይታሰባል። አላህ እንዲህ እንዳለው: {በዚያች እርሷ መልካም በሆነችው ጸባይ (መጥፎይቱን) ገፍትር። ያን ጊዜ ያ ባንተና በእርሱ መካከል ጠብ ያለው ሰው ልክ እንደ አዛኝ ዘመድ ይሆናል።}
ጉዳት እየደረሰበት ራሱ የአላህን ትእዛዝ መስራቱ አማኙ ባሪያ የአላህን እገዛ እንዲያገኝ ምክንያት ይሆነዋል።
ዝምድና መቁረጥ በዱንያ ቅጣትና ህመም በመጪው አለም ደግሞ ወንጀልና ሒሳብ ይጠብቀዋል።
አንድ ሙስሊም በመልካም ስራው ምንዳውን ማሰብ ይገባዋል። መልካም ስራውን ከመስራትም የሰዎች ማወክና ማደናቀፍ ከመልካም ልማዱ አያቋርጠውም።
ዝምድናን ከቀጠሉት ጋር ውለታን የሚመልስ ዝምድና ቀጣይ አይባልም። ነገር ግን ትክክለኛ ዝምድና ቀጣይ የሚባለው ዝምድናው የተቆረጠች ጊዜ የሚቀጥላት ነው።
ጉዳት እየደረሰበት ራሱ የአላህን ትእዛዝ መስራቱ አማኙ ባሪያ የአላህን እገዛ እንዲያገኝ ምክንያት ይሆነዋል።
ዝምድና መቁረጥ በዱንያ ቅጣትና ህመም በመጪው አለም ደግሞ ወንጀልና ሒሳብ ይጠብቀዋል።
አንድ ሙስሊም በመልካም ስራው ምንዳውን ማሰብ ይገባዋል። መልካም ስራውን ከመስራትም የሰዎች ማወክና ማደናቀፍ ከመልካም ልማዱ አያቋርጠውም።
ዝምድናን ከቀጠሉት ጋር ውለታን የሚመልስ ዝምድና ቀጣይ አይባልም። ነገር ግን ትክክለኛ ዝምድና ቀጣይ የሚባለው ዝምድናው የተቆረጠች ጊዜ የሚቀጥላት ነው።
Attribution
[ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

