የቂያማ ቀን በኔ አማላጅነት ከሰዎች ሁሉ ይበልጥ እድለኛ የሚሆኑት ጥርት ባለ መልኩ ከልባቸው ወይም ከነፍሳቸው 'ላ ኢላሃ ኢለሏህ' ያሉት ናቸው።'
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተለለፈው እንዲህ ብለዋል: "የአላህ መልእክተኛ ሆይ! የቂያማ ቀን በርሶ ምልጃ ከሰዎች ሁሉ ይበልጥ እድለኛው ማን ነው?" ተባሉ። የአላህ መልክተኛም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ አሉ፡- 'አቡ ሁረይራ ሆይ! ባንተ ላይ ካየሁት የሐዲሥ ጉጉት አንፃር ይህንን ጥያቄ ለመጠየቅ የሚቀድምህ አይኖርም ብዬ አስቤ ነበር። የቂያማ ቀን በኔ አማላጅነት ከሰዎች ሁሉ ይበልጥ እድለኛ የሚሆኑት ጥርት ባለ መልኩ ከልባቸው ወይም ከነፍሳቸው 'ላ ኢላሃ ኢለሏህ' ያሉት ናቸው።'"
Explanation
Benefits
የነቢዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ሸፋዓ (ምልጃ) ተውሒድ ላይ እያለ (በኃጢዓቱ ምክንያት) ጀሀነም የተፈረደበትን ወደ ጀሀነም እንዳይገባ፤ ከገባ ደግሞ እንዲወጣ የሚያደርጉት ምልጃ ነው፤
ለአላህ ጥርት ተደርጋ የተባለች የተውሒድ ቃል ያላት ትሩፋትና የምታሳድረውን ከፍተኛ ተጽዕኖ እንረዳለን።
የተውሒድ ቃል የሚረጋገጠው ትርጉሟን በማወቅና የምታስፈርደውን ተግባራዊ በማድረግ ነው።
አቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና - ያላቸውን ደረጃና በዕውቀት ላይ ያላቸውን ጉጉት እንረዳለን።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

