HadeethEnc · 1.23.0
በአማኞች ላይ ወይም በኡመቴ ላይ እንዳይከብዳቸው ብዬ ነው እንጂ በሁሉም ሶላቶች ወቅት መፋቂያ እንዲጠቀሙ አዛቸው ነበር።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፦ "በአማኞች ላይ ወይም በኡመቴ ላይ እንዳይከብዳቸው ብዬ ነው እንጂ በሁሉም ሶላቶች ወቅት መፋቂያ እንዲጠቀሙ አዛቸው ነበር።"
02
Explanation
ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከኡመታቸው መካከል አማኞች ለሆኑት እንዳይከብድባቸው ባይሰጉላቸው ኖሮ ከሁሉም ሶላቶች ጋር መፋቂያን መጠቀም ግዴታ ያደርጉት እንደነበር ተናገሩ።
03
Benefits
ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና በኡመታቸው ላይ ያላቸው እዝነትና እንዳይከብድባቸውም የሚጠነቀቁላቸው መሆናቸውን እንረዳለን።
የነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ትእዛዝ ሱና መሆኑን የሚጠቁም ማስረጃ እስካልመጣ ድረስ በመሰረቱ ግዴታ ነው።
ሁሉም ሶላት ዘንድ የመፋቅን ተወዳጅነትና ያለውን ትሩፋት እንረዳለን።
ኢብኑ ደቂቅ አልዒድ እንዲህ ብለዋል: «ወደ ሶላት በሚቆም ወቅት መፋቅ የተወደደበት ጥበብ ሶላት ወደ አላህ መቃረቢያ ወቅት ስለሆነ ነው። ይህ ደሞ አምልኮውን ማላቅህን ለማንፀባረቅ ሲባል የተሟላ ሁኔታንና ንፁህ መሆንን ይጠይቃል።»
የሐዲሡ ጥቅል ሀሳብ ፆመኛ እንኳን ቢሆን ፀሃይ ዘንበል ካለች በኋላም መፋቁ እንደሚወደድለት ያካትታል። (ፆመኛ ሁኖ) በዙህርና ዐስር ሶላት ወቅት መፋቅን ይመስል።
የነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ትእዛዝ ሱና መሆኑን የሚጠቁም ማስረጃ እስካልመጣ ድረስ በመሰረቱ ግዴታ ነው።
ሁሉም ሶላት ዘንድ የመፋቅን ተወዳጅነትና ያለውን ትሩፋት እንረዳለን።
ኢብኑ ደቂቅ አልዒድ እንዲህ ብለዋል: «ወደ ሶላት በሚቆም ወቅት መፋቅ የተወደደበት ጥበብ ሶላት ወደ አላህ መቃረቢያ ወቅት ስለሆነ ነው። ይህ ደሞ አምልኮውን ማላቅህን ለማንፀባረቅ ሲባል የተሟላ ሁኔታንና ንፁህ መሆንን ይጠይቃል።»
የሐዲሡ ጥቅል ሀሳብ ፆመኛ እንኳን ቢሆን ፀሃይ ዘንበል ካለች በኋላም መፋቁ እንደሚወደድለት ያካትታል። (ፆመኛ ሁኖ) በዙህርና ዐስር ሶላት ወቅት መፋቅን ይመስል።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

