ለወንዶች ምርጡ የሶላት ሰልፍ የመጀመሪያው ሰልፍ ነው። መጥፎው ደግሞ የመጨረሻው ነው። ለሴቶች ምርጡ ሰልፍ የመጨረሻው ሰልፍ ነው። መጥፎው ደግሞ የመጀመሪያው ነው።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል: "ለወንዶች ምርጡ የሶላት ሰልፍ የመጀመሪያው ሰልፍ ነው። መጥፎው ደግሞ የመጨረሻው ነው። ለሴቶች ምርጡ ሰልፍ የመጨረሻው ሰልፍ ነው። መጥፎው ደግሞ የመጀመሪያው ነው።"
Explanation
Benefits
ሴቶች ራሱን በቻለ ሰልፍ ከወንዶች ጋር መስጂድ ውስጥ መስገድ እንደሚፈቀድላቸው እንረዳለን። ነገር ግን ከመሸፋፈንና ከመከናነብ ጋር ነው።
ሴቶች መስጂድ ውስጥ ከተሰባሰቡ ልክ እንደ ወንዶች ሰልፍ ሰልፎች ይሰራሉ እንጂ አይበታተኑም። ይልቁንም ያለባቸው ግዴታ ልክ እንደ ወንዶቹ ሰልፍ ሶፋቸውን ማስተካል፣ ጉድለትን መሙላት ነው።
ሸሪዓ በአምልኮ ስፍራ ሳይቀር ሴቶች ከወንዶች እንዲርቁ በማነሳሳቱ (ለአለመቀላቀል) ከፍተኛ ትኩረት እንደሰጠ ግልፅ ያደርግልናል።
ሰዎች በስራቸው ልክ እንደሚበላለጡ እንረዳለን።
ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: «የወንዶች ሰልፍ ላይ የተነገረው መልዕክት በጥቅሉ ነው የሚወሰደው። መቼም ቢሆን የወንዶች ምርጡ ሰልፍ የመጀመሪያው ነው። መጥፎው ደግሞ የመጨረሻው ነው። የሴቶች ሰልፍ ግን ሐዲሡ ላይ የተፈለገው: ከወንዶች ጋር የሚሰግዱ ሴቶችን ነው የሚመለከተው። ከወንዶች ውጪ ተለይተው ለብቻቸው ከሰገዱ ግን የነርሱም ብይን እንደወንዶቹ ነው የሚሆነው። ማለትም ምርጡ ሰልፍ የመጀመሪያው መጥፎው ደግሞ የመጨረሻው ነው የሚሆነው።»
ነወዊይ እንዲህም ብለዋል: «በሐዲሥ ውስጥ ስለሚያስገኘው ደረጃ ተወድሶ የመጣውና የተበረታታው የመጀመሪያው ሰልፍ ሰጋጁ መጀመሪያም መጣ ዘግይቶ መጣ፣ በመካከል ግርዶሽና የመሳሰሉት ቢገባም ባይገባም ኢማሙን የሚቀጥለው ሰልፍ ነው።»
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

