ረመዳን የገባ ጊዜ የጀነት በሮች ይከፈታሉ፤ የእሳት በሮችም ይዘጋሉ፤ ሰይጣኖችም ይጠፈነጋሉ።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ ብለዋል፦ "ረመዳን የገባ ጊዜ የጀነት በሮች ይከፈታሉ፤ የእሳት በሮችም ይዘጋሉ፤ ሰይጣኖችም ይጠፈነጋሉ።"
Explanation
Benefits
ይህ የተከበረ ወር የአምልኮና የመልካም ተግባር ወቅት ከመሆኑ አኳያ ይህ ሐዲሥ ለጾመኞች ብስራት ነው።
ረመዷን ውስጥ ሸይጣኖች መጠፍነጋቸው የትኛውም ለአቅመ አዳም የደረሰ ሰው ወንጀል ለመስራት ምክንያት እንደሌለው ለመጠቆም ነው። "ሸይጣኖች ወደ አንተ እንዳይቀርቡ ስለተጠበቅክ አምልኮ ለመተውህና ወንጀልን ለመስራትህ እነርሱን ምክንያት እንዳታደርግ።" የተባለ ነው የሚመስለው።
ቁርጡቢይ እንዲህ ብለዋል: «"በረመዳን ውስጥ ብዙ ክፋትና ወንጀሎች ሲከሰት እንዴት እናያለን? ሸይጣኖች ቢታሰሩ ኖሮ ይህ አይከሰትም ነበር።" ቢባል። መልሱ: ክፋቶችና ወንጀሎች የሚያንሱት መስፈርቶቹን የጠበቀና ስነስርዓቱን ያሟላን ጾም ከጾሙ ሰዎች ላይ ነው። ወይም የሚታሰሩት በአንዳንድ ዘገባዎች ቀደም ተብሎ እንደተጠቀሰው ሁሉም ሳይሆኑ አመፀኛ የሆኑት የተወሰኑ ሸይጣኖች ብቻ ናቸው። ወይም በሐዲሡ የተፈለገው ክፋቶች እንደሚያንሱ መጥቀስ ነው። ይህም ደግሞ በገሃድ የሚታይ ነገር ነው። ከሌላ ጊዜ በተለየ ወንጀሎች በረመዷን መከሰታቸው እጅግ የመነመነ ነውና። በተጨማሪም ሁሉም ሸይጣኖች በመታሰራቸው ክፋትና ወንጀል አይከሰትም የሚለውን አያሲዝም። ወንጀል ለመስራት እንደ ቆሸሸች ነፍስ፣ መጥፎ ልምዶችና የሰው ሸይጣኖችን የመሰሉ ከጂን ሸይጣን ውጪ ያሉ ሌሎች ምክንያቶችም ስላሉ።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

