الإنفطار

 

Al-Infitar

 

The Cleaving

1 - Al-Infitar (The Cleaving) - 001

إِذَا ٱلسَّمَآءُ ٱنفَطَرَتۡ
ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤

2 - Al-Infitar (The Cleaving) - 002

وَإِذَا ٱلۡكَوَاكِبُ ٱنتَثَرَتۡ
ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤

3 - Al-Infitar (The Cleaving) - 003

وَإِذَا ٱلۡبِحَارُ فُجِّرَتۡ
ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤

4 - Al-Infitar (The Cleaving) - 004

وَإِذَا ٱلۡقُبُورُ بُعۡثِرَتۡ
መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤

5 - Al-Infitar (The Cleaving) - 005

عَلِمَتۡ نَفۡسٞ مَّا قَدَّمَتۡ وَأَخَّرَتۡ
ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡

6 - Al-Infitar (The Cleaving) - 006

يَـٰٓأَيُّهَا ٱلۡإِنسَٰنُ مَا غَرَّكَ بِرَبِّكَ ٱلۡكَرِيمِ
አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?

7 - Al-Infitar (The Cleaving) - 007

ٱلَّذِي خَلَقَكَ فَسَوَّىٰكَ فَعَدَلَكَ
በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡

8 - Al-Infitar (The Cleaving) - 008

فِيٓ أَيِّ صُورَةٖ مَّا شَآءَ رَكَّبَكَ
በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡

9 - Al-Infitar (The Cleaving) - 009

كَلَّا بَلۡ تُكَذِّبُونَ بِٱلدِّينِ
ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡

10 - Al-Infitar (The Cleaving) - 010

وَإِنَّ عَلَيۡكُمۡ لَحَٰفِظِينَ
በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤

11 - Al-Infitar (The Cleaving) - 011

كِرَامٗا كَٰتِبِينَ
የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡

12 - Al-Infitar (The Cleaving) - 012

يَعۡلَمُونَ مَا تَفۡعَلُونَ
የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡

13 - Al-Infitar (The Cleaving) - 013

إِنَّ ٱلۡأَبۡرَارَ لَفِي نَعِيمٖ
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡

14 - Al-Infitar (The Cleaving) - 014

وَإِنَّ ٱلۡفُجَّارَ لَفِي جَحِيمٖ
ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡

15 - Al-Infitar (The Cleaving) - 015

يَصۡلَوۡنَهَا يَوۡمَ ٱلدِّينِ
በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡

16 - Al-Infitar (The Cleaving) - 016

وَمَا هُمۡ عَنۡهَا بِغَآئِبِينَ
እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡

17 - Al-Infitar (The Cleaving) - 017

وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ
የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

18 - Al-Infitar (The Cleaving) - 018

ثُمَّ مَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ
ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

19 - Al-Infitar (The Cleaving) - 019

يَوۡمَ لَا تَمۡلِكُ نَفۡسٞ لِّنَفۡسٖ شَيۡـٔٗاۖ وَٱلۡأَمۡرُ يَوۡمَئِذٖ لِّلَّهِ
(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡

Scroll to Top