النجم
An-Najm
The Star
1 - An-Najm (The Star) - 001
وَٱلنَّجۡمِ إِذَا هَوَىٰ
በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡
2 - An-Najm (The Star) - 002
مَا ضَلَّ صَاحِبُكُمۡ وَمَا غَوَىٰ
ባልደረባችሁ (ነቢያችን ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡
3 - An-Najm (The Star) - 003
وَمَا يَنطِقُ عَنِ ٱلۡهَوَىٰٓ
ከልብ ወለድም አይናገርም፡፡
4 - An-Najm (The Star) - 004
إِنۡ هُوَ إِلَّا وَحۡيٞ يُوحَىٰ
እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
5 - An-Najm (The Star) - 005
عَلَّمَهُۥ شَدِيدُ ٱلۡقُوَىٰ
ኀይሎቹ ብርቱው አስተማረው፡፡
6 - An-Najm (The Star) - 006
ذُو مِرَّةٖ فَٱسۡتَوَىٰ
የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡
7 - An-Najm (The Star) - 007
وَهُوَ بِٱلۡأُفُقِ ٱلۡأَعۡلَىٰ
እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡
8 - An-Najm (The Star) - 008
ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ
ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም፡፡
9 - An-Najm (The Star) - 009
فَكَانَ قَابَ قَوۡسَيۡنِ أَوۡ أَدۡنَىٰ
(ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡
10 - An-Najm (The Star) - 010
فَأَوۡحَىٰٓ إِلَىٰ عَبۡدِهِۦ مَآ أَوۡحَىٰ
ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡
11 - An-Najm (The Star) - 011
مَا كَذَبَ ٱلۡفُؤَادُ مَا رَأَىٰٓ
(ነቢዩም በዓይኑ) ያየውን ልቡ አልዋሸም፡፡
12 - An-Najm (The Star) - 012
أَفَتُمَٰرُونَهُۥ عَلَىٰ مَا يَرَىٰ
ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?
13 - An-Najm (The Star) - 013
وَلَقَدۡ رَءَاهُ نَزۡلَةً أُخۡرَىٰ
በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡
14 - An-Najm (The Star) - 014
عِندَ سِدۡرَةِ ٱلۡمُنتَهَىٰ
በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤
15 - An-Najm (The Star) - 015
عِندَهَا جَنَّةُ ٱلۡمَأۡوَىٰٓ
እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡
16 - An-Najm (The Star) - 016
إِذۡ يَغۡشَى ٱلسِّدۡرَةَ مَا يَغۡشَىٰ
ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡
17 - An-Najm (The Star) - 017
مَا زَاغَ ٱلۡبَصَرُ وَمَا طَغَىٰ
ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡
18 - An-Najm (The Star) - 018
لَقَدۡ رَأَىٰ مِنۡ ءَايَٰتِ رَبِّهِ ٱلۡكُبۡرَىٰٓ
ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ፡፡
19 - An-Najm (The Star) - 019
أَفَرَءَيۡتُمُ ٱللَّـٰتَ وَٱلۡعُزَّىٰ
አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?
20 - An-Najm (The Star) - 020
وَمَنَوٰةَ ٱلثَّالِثَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰٓ
ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?) (የላቸውም)።
21 - An-Najm (The Star) - 021
أَلَكُمُ ٱلذَّكَرُ وَلَهُ ٱلۡأُنثَىٰ
ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?
22 - An-Najm (The Star) - 022
تِلۡكَ إِذٗا قِسۡمَةٞ ضِيزَىٰٓ
ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍፍል ናት፡፡
23 - An-Najm (The Star) - 023
إِنۡ هِيَ إِلَّآ أَسۡمَآءٞ سَمَّيۡتُمُوهَآ أَنتُمۡ وَءَابَآؤُكُم مَّآ أَنزَلَ ٱللَّهُ بِهَا مِن سُلۡطَٰنٍۚ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّ وَمَا تَهۡوَى ٱلۡأَنفُسُۖ وَلَقَدۡ جَآءَهُم مِّن رَّبِّهِمُ ٱلۡهُدَىٰٓ
እነርሱ እናንተና አባቶቻችሁ (አማልክት ብላችሁ) የጠራችኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፡፡ አላህ በእርሷ (መግገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ከጌታቸውም መምሪያ የመጣላቸው ሲኾኑ ጥርጣሬንና ነፍሶች የሚዘነበሉበትን እንጅ ሌላ አይከተሉም፡፡
24 - An-Najm (The Star) - 024
أَمۡ لِلۡإِنسَٰنِ مَا تَمَنَّىٰ
ለሰው የተመኘው ሁሉ አለውን?
25 - An-Najm (The Star) - 025
فَلِلَّهِ ٱلۡأٓخِرَةُ وَٱلۡأُولَىٰ
መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም (ዓለም) የአላህ ብቻ ናቸው፡፡
26 - An-Najm (The Star) - 026
۞وَكَم مِّن مَّلَكٖ فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ لَا تُغۡنِي شَفَٰعَتُهُمۡ شَيۡـًٔا إِلَّا مِنۢ بَعۡدِ أَن يَأۡذَنَ ٱللَّهُ لِمَن يَشَآءُ وَيَرۡضَىٰٓ
በሰማያት ውስጥ ካለ መልአክም ብዙዎች (ሊማለዱለት) ለሚሻውና ለሚወደው ሰው ከፈቀደ በኋላ ቢኾን እንጅ ምልጃቸው ምንም አትጠቅምም፡፡
27 - An-Najm (The Star) - 027
إِنَّ ٱلَّذِينَ لَا يُؤۡمِنُونَ بِٱلۡأٓخِرَةِ لَيُسَمُّونَ ٱلۡمَلَـٰٓئِكَةَ تَسۡمِيَةَ ٱلۡأُنثَىٰ
እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡
28 - An-Najm (The Star) - 028
وَمَا لَهُم بِهِۦ مِنۡ عِلۡمٍۖ إِن يَتَّبِعُونَ إِلَّا ٱلظَّنَّۖ وَإِنَّ ٱلظَّنَّ لَا يُغۡنِي مِنَ ٱلۡحَقِّ شَيۡـٔٗا
ለእነርሱም በእርሱ ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ ጥርጣሬን እንጅ ሌላን አይከተሉም፡፡ ጥርጣሬም ከእውነት ምንም አያብቃቃም፡፡
29 - An-Najm (The Star) - 029
فَأَعۡرِضۡ عَن مَّن تَوَلَّىٰ عَن ذِكۡرِنَا وَلَمۡ يُرِدۡ إِلَّا ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
ከግሣጼያችንም (ከቁርኣን) ከሸሸና አነስተኛይቱን ሕይወት እንጅ ሌላን ከማይሻ ሰው ዙር (ተወው)፡፡
30 - An-Najm (The Star) - 030
ذَٰلِكَ مَبۡلَغُهُم مِّنَ ٱلۡعِلۡمِۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ وَهُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱهۡتَدَىٰ
ይህ (አነስተኛይቱን ሕይወት መምረጥ) ከዕውቀት ድካቸው ነው፡፡ ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን በእርግጥ ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም የቀናውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
31 - An-Najm (The Star) - 031
وَلِلَّهِ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِي ٱلۡأَرۡضِ لِيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَسَـٰٓـُٔواْ بِمَا عَمِلُواْ وَيَجۡزِيَ ٱلَّذِينَ أَحۡسَنُواْ بِٱلۡحُسۡنَى
በሰማያት ያለውና በምድር ያለው ሁሉ የአላህ ነው፡፡ እነዚያን ያጠፉትን በሠሩት ሊመነዳ (ሊቀጣ) እነዚያን ያሳመሩትንም በመልካሚቱ (ገነት) ሊመነዳ (ነው)፡፡
32 - An-Najm (The Star) - 032
ٱلَّذِينَ يَجۡتَنِبُونَ كَبَـٰٓئِرَ ٱلۡإِثۡمِ وَٱلۡفَوَٰحِشَ إِلَّا ٱللَّمَمَۚ إِنَّ رَبَّكَ وَٰسِعُ ٱلۡمَغۡفِرَةِۚ هُوَ أَعۡلَمُ بِكُمۡ إِذۡ أَنشَأَكُم مِّنَ ٱلۡأَرۡضِ وَإِذۡ أَنتُمۡ أَجِنَّةٞ فِي بُطُونِ أُمَّهَٰتِكُمۡۖ فَلَا تُزَكُّوٓاْ أَنفُسَكُمۡۖ هُوَ أَعۡلَمُ بِمَنِ ٱتَّقَىٰٓ
(እነርሱ) እነዚያ የኃጢኣትን ታላለቆችና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ (የሚማሩ) ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ሆዶች ውስጥ ሽሎች በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በናንተ (ኹነታ) ዐዋቂ ነው፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታወድሱ እርሱ የሚፈራውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
33 - An-Najm (The Star) - 033
أَفَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي تَوَلَّىٰ
ያንን (ከእምነት) የዞረውን አየህን?
34 - An-Najm (The Star) - 034
وَأَعۡطَىٰ قَلِيلٗا وَأَكۡدَىٰٓ
ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)
35 - An-Najm (The Star) - 035
أَعِندَهُۥ عِلۡمُ ٱلۡغَيۡبِ فَهُوَ يَرَىٰٓ
የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?
36 - An-Najm (The Star) - 036
أَمۡ لَمۡ يُنَبَّأۡ بِمَا فِي صُحُفِ مُوسَىٰ
ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?
37 - An-Najm (The Star) - 037
وَإِبۡرَٰهِيمَ ٱلَّذِي وَفَّىٰٓ
በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)
38 - An-Najm (The Star) - 038
أَلَّا تَزِرُ وَازِرَةٞ وِزۡرَ أُخۡرَىٰ
(እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡
39 - An-Najm (The Star) - 039
وَأَن لَّيۡسَ لِلۡإِنسَٰنِ إِلَّا مَا سَعَىٰ
ለሰውም ሁሉ የሠራው እንጅ ሌላ የለውም፡፡
40 - An-Najm (The Star) - 040
وَأَنَّ سَعۡيَهُۥ سَوۡفَ يُرَىٰ
ሥራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል፡፡
41 - An-Najm (The Star) - 041
ثُمَّ يُجۡزَىٰهُ ٱلۡجَزَآءَ ٱلۡأَوۡفَىٰ
ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡
42 - An-Najm (The Star) - 042
وَأَنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلۡمُنتَهَىٰ
መጨረሻውም ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
43 - An-Najm (The Star) - 043
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَضۡحَكَ وَأَبۡكَىٰ
እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡
44 - An-Najm (The Star) - 044
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَمَاتَ وَأَحۡيَا
እነሆ እርሱም ገደለ፣ አስነሳም፡፡
45 - An-Najm (The Star) - 045
وَأَنَّهُۥ خَلَقَ ٱلزَّوۡجَيۡنِ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰ
እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡
46 - An-Najm (The Star) - 046
مِن نُّطۡفَةٍ إِذَا تُمۡنَىٰ
ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡
47 - An-Najm (The Star) - 047
وَأَنَّ عَلَيۡهِ ٱلنَّشۡأَةَ ٱلۡأُخۡرَىٰ
የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡
48 - An-Najm (The Star) - 048
وَأَنَّهُۥ هُوَ أَغۡنَىٰ وَأَقۡنَىٰ
እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡
49 - An-Najm (The Star) - 049
وَأَنَّهُۥ هُوَ رَبُّ ٱلشِّعۡرَىٰ
እነሆ እርሱም የሺዕራ ጌታ ነው፡፡
50 - An-Najm (The Star) - 050
وَأَنَّهُۥٓ أَهۡلَكَ عَادًا ٱلۡأُولَىٰ
እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡
51 - An-Najm (The Star) - 051
وَثَمُودَاْ فَمَآ أَبۡقَىٰ
ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡
52 - An-Najm (The Star) - 052
وَقَوۡمَ نُوحٖ مِّن قَبۡلُۖ إِنَّهُمۡ كَانُواْ هُمۡ أَظۡلَمَ وَأَطۡغَىٰ
በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡
53 - An-Najm (The Star) - 053
وَٱلۡمُؤۡتَفِكَةَ أَهۡوَىٰ
የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡
54 - An-Najm (The Star) - 054
فَغَشَّىٰهَا مَا غَشَّىٰ
ያለበሳትንም አለበሳት፡፡
55 - An-Najm (The Star) - 055
فَبِأَيِّ ءَالَآءِ رَبِّكَ تَتَمَارَىٰ
ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?
56 - An-Najm (The Star) - 056
هَٰذَا نَذِيرٞ مِّنَ ٱلنُّذُرِ ٱلۡأُولَىٰٓ
ይህ ከፊተኞቹ አስፈራሪዎች (ጎሳ) የኾነ አስፈራሪ ነው፡፡
57 - An-Najm (The Star) - 057
أَزِفَتِ ٱلۡأٓزِفَةُ
ቀራቢይቱ (ኅልፈተ ዓለም) ቀረበች፡፡
58 - An-Najm (The Star) - 058
لَيۡسَ لَهَا مِن دُونِ ٱللَّهِ كَاشِفَةٌ
ለእርሷ ከአላህ ሌላ ገላጭ የላትም፡፡
59 - An-Najm (The Star) - 059
أَفَمِنۡ هَٰذَا ٱلۡحَدِيثِ تَعۡجَبُونَ
ከዚህ ንግግር ትደነቃላችሁን?
60 - An-Najm (The Star) - 060
وَتَضۡحَكُونَ وَلَا تَبۡكُونَ
ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን?
61 - An-Najm (The Star) - 061
وَأَنتُمۡ سَٰمِدُونَ
እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡
62 - An-Najm (The Star) - 062