አንዲት ሴት ከባሏ ውጪ ለሞተባት ሰው ሀዘንን ለመግለፅ ብላ ከሶስት ቀን በላይ መዋብን አትተው። የሞተባት ባሏ ከሆነ ግን አራት ወር ከአስር ቀን ከመዋብ ትታቀብ።
ከኡሙ ዐጢየህ - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው: የአላህ መልክተኛ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል: "አንዲት ሴት ከባሏ ውጪ ለሞተባት ሰው ሀዘንን ለመግለፅ ብላ ከሶስት ቀን በላይ መዋብን አትተው። የሞተባት ባሏ ከሆነ ግን አራት ወር ከአስር ቀን ከመዋብ ትታቀብ። (ለባሏ ሀዘን ስትቀመጥ) ከስፌት በፊት የተቀለመን ልብስ ካልሆነ በቀር በቀለም ያጌጠን ልብስ አትልበስ፣…

