አንዳችን ነገር ከኛ ሰምቶ እንደሰማው አድርጎ ያደረሰ ሰው አላህ ያብራው። ከሰማው ሰው የበለጠ (የሰማውን አብልጦ) የሚጠብቅ ስንትና ስንት ሰው አለ!
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከዐብደላህ ቢን መስዑድ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ: "አንዳችን ነገር ከኛ ሰምቶ እንደሰማው አድርጎ ያደረሰ ሰው አላህ ያብራው። ከሰማው ሰው የበለጠ (የሰማውን አብልጦ) የሚጠብቅ ስንትና ስንት ሰው አለ!"
Explanation
Benefits
የሐዲሥ ምሁራኖች ያላቸው ደረጃና ሐዲሥን የመፈለግ ልቅና መገለፁ፤
የግንዛቤ ባለቤቶች የሆኑት ዑለማዎች ያላቸው ደረጃን እንረዳለን።
ሶሐቦች (ሪድዋኑሏሁ ዐለይሂም) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ከአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ሐዲሥን ሰምተው ለኛ ማድረሳቸው የነርሱን ደረጃ ያስረዳናል።
አልመናዊ እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ ሐዲሥን ለማስተላለፍ ሐዲሡን ፈቂህ (መገንዘብ) መስፈርት እንዳልሆነ ገለፆልናል። ሐዲሥ ለማስተላለፍ መስፈርቱ መሸምደድ ነው። ፈቂህ (በደንብ ተገንዛቢ) የሆነ ሰው ደግሞ ሐዲሡን መገንዘብና ማስተንተን ይገባዋል።"
ኢብኑ ዑየይናህ እንዲህ ብለዋል: "ሐዲሥን የሚፈልግ ሰው ሁሉ በዚህ ሐዲሥ መሰረት ፊቱ ላይ ብርሃን አለው።"
የሐዲሥ ሊቃውንቶች ዘንድ ሽምደዳ ሁለት አይነት ነው: እነርሱም: በቀልብ መሸምደድ እና በመጽሐፍና በጽሑፍ መጠበቅ ነው። ሁለቱንም ሐዲሡ ውስጥ የተጠቀሰው ዱዓእ ይጠቀልላቸዋል።
የሰዎች ግንዛቤ ይበላለጣል። አንዳንድ ሐዲሥ የደረሳቸው መጀመርያ ከሰማው የበለጠ ተገንዛቢ ሊሆኑ ይችላሉ፤ ፊቂህን የተሸከሙ ሆነው (ፈቂህ ያልሆኑ) ግንዛቤ የሌላቸውም ስንትና ስንት ሰዎች ይኖራሉ?!
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

