HadeethEnc · 1.23.0
አማና (አደራ) የሌለው ሰው ኢማን የለውም፤ ቃልኪዳን የማያከብር የሆነ ሰው ሃይማኖት የለውም።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአነስ ቢን ማሊክ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ ነቢይ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዲህ ሳይሉን አንድም ኹጥባ አያደርጉም ነበር: "አማና (አደራ) የሌለው ሰው ኢማን የለውም፤ ቃልኪዳን የማያከብር የሆነ ሰው ሃይማኖት የለውም።"»
02
Explanation
አነስ ቢን ማሊክ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ ብለው ተናገሩ: ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ኹጥባ ሲያደርጉ ወይም ሲመክሩ ሁለት ነገሮችን ሳይጠቅሱ የሚያልፉበት ጊዜ በጣም ጥቂት ጊዜያት ነው። የመጀመሪያው: አንድን አካል በገንዘብ ወይም በነፍስ ወይም በቤተሰብ ጉዳይ ነፍሱ ውስጥ ከዳተኝነት ያለችበት ሰው የተሟላ ኢማን የለውም። ሁለተኛው: ቃልኪዳንን የሚያፈርስ ሰው የተሟላ ሃይማኖት የለውም።
03
Benefits
አደራን በመወጣት ላይና ቃልኪዳንን በመሙላት ላይ መነሳሳቱን እንረዳለን። እነዚህን ሁለት ነገሮች ማፍረስ ኢማንን ያፈርሳል።
አደራን ከመካድና ቃልኪዳንን ከማፍረስ መከልከሉንና እነዚህን መፈፀምም ከትላልቅ ወንጀሎች እንደሆነ እንረዳለን።
ሐዲሡ በአላህና በባሪያው መካከል ያለንም ይሁን ፍጡራን እርስ በርሳቸው መካከል ያለውንም አደራ መጠበቅንና ቃልኪዳን ማክበርን ያካትታል።
አደራን ከመካድና ቃልኪዳንን ከማፍረስ መከልከሉንና እነዚህን መፈፀምም ከትላልቅ ወንጀሎች እንደሆነ እንረዳለን።
ሐዲሡ በአላህና በባሪያው መካከል ያለንም ይሁን ፍጡራን እርስ በርሳቸው መካከል ያለውንም አደራ መጠበቅንና ቃልኪዳን ማክበርን ያካትታል።
Attribution
[አሕመድ ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

