HadeethEnc · 1.23.0
ከኡመቴ መካከል የበላይ የሆኑ ጭፍሮች (ከመኖር) አይወገዱም። የአላህ ትእዛዝ እስኪመጣባቸው ድረስም የበላይ እንደሆኑ ይቆያሉ።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከሙጊራ ቢን ሹዕባ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ ብለዋል፦ "ከኡመቴ መካከል የበላይ የሆኑ ጭፍሮች (ከመኖር) አይወገዱም። የአላህ ትእዛዝ እስኪመጣባቸው ድረስም የበላይ እንደሆኑ ይቆያሉ።"
02
Explanation
ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ከኡመቴ መካከል በሰዎች ላይ የበላይ የሆኑ፣ በተፃረራቸው ላይ አሸናፊዎች የሆኑ ህዝቦች ከመኖር አይወገዱም። ይህ የበላይነታቸው የሚቆየውም ትንሳኤ ከመቆሙ በፊት የዱንያ መጨረሻ ዘመን ላይ ነፍሳቸው እንድትወጣ የሚመጣው የአላህ ትእዛዝ እስኪመጣ ድረስ መሆኑን ተናገሩ።
03
Benefits
የነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ግልፅ ተአምርን እንመለከታለን። ይህ መገለጫ ለአላህ ምስጋና ይግባውና ከነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ከመኖር አልተወገደምና። ሐዲሡ ውስጥ የተጠቀሰው የአላህ ትእዛዝ እስኪመጣ ድረስም ከመኖር አይወገድም።
በሐቅ ላይ የመፅናትና በርሱም የመስራት ትሩፋትን በዚህ ላይም መነሳሳቱን እንረዳለን።
የዲን የበላይነት ሁለት አይነት ነው: ወይ የማስረጃና እውነታን የማብራራት የበላይነት ነው። ወይም የሀይልና የመሳሪያ የበላይነት ነው። የማስረጃና ማብራራት የበላይነት ዘውትር ያለ ጉዳይ ነው። ምክንያቱም የእስልምና ማስረጃ ቁርአን ነውና። ቁርአን ደግሞ ከርሱ ውጪ ባሉት ላይ ሁሌ የበላይና አሸናፊ ነው። ነገር ግን ሁለተኛው የበላይነት አይነት ማለትም የሀይልና የመሳሪያ የበላይነት በኢማንና በምድር እንደሚኖር መመቻቸት መጠን የሚወሰን ነው።
በሐቅ ላይ የመፅናትና በርሱም የመስራት ትሩፋትን በዚህ ላይም መነሳሳቱን እንረዳለን።
የዲን የበላይነት ሁለት አይነት ነው: ወይ የማስረጃና እውነታን የማብራራት የበላይነት ነው። ወይም የሀይልና የመሳሪያ የበላይነት ነው። የማስረጃና ማብራራት የበላይነት ዘውትር ያለ ጉዳይ ነው። ምክንያቱም የእስልምና ማስረጃ ቁርአን ነውና። ቁርአን ደግሞ ከርሱ ውጪ ባሉት ላይ ሁሌ የበላይና አሸናፊ ነው። ነገር ግን ሁለተኛው የበላይነት አይነት ማለትም የሀይልና የመሳሪያ የበላይነት በኢማንና በምድር እንደሚኖር መመቻቸት መጠን የሚወሰን ነው።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

