HadeethEnc · 1.23.0
አንድ ሰውዬ ዓደን አብየን ላይ ሆኖ እንኳ ሐረም ውስጥ በደል ለመስራት ቢያስብ አላህ አሳማሚ ቅጣትን ያቀምሰዋል።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ዐብደላህ ቢን መስዑድ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- ከነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- እንዳስተላለፈው {በእርሱም ውስጥ (ከትክክለኛ መንገድ) በመዘንበል በዳይ ሆኖ (ማንኛውንም ነገር) የሚፈልግ ሰው ከአሳማሚ ቅጣት እናቀምሰዋለን።} [አልሐጅ: 25] በሚለው የአላህ ንግግር ዙሪያ እንዲህ ብለዋል: "አንድ ሰውዬ ዓደን አብየን ላይ ሆኖ እንኳ ሐረም ውስጥ በደል ለመስራት ቢያስብ አላህ አሳማሚ ቅጣትን ያቀምሰዋል።"
02
Explanation
ዐብደላህ ቢን መስዑድ ረዲየሏሁ ዐንሁ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - {በእርሱም ውስጥ (ከትክክለኛ መንገድ) በመዘንበል በዳይ ሆኖ (ማንኛውንም ነገር) የሚፈልግ ሰው ከአሳማሚ ቅጣት እናቀምሰዋለን።} [አልሐጅ: 25] በሚለው የአላህ ቃል ዙሪያ እንዲህ ማለታቸውን ገለፀ: "አንድ ሰው በሐረም መካ ላይ በምላስ ወይም ሆን ብሎ በመግደል አላህ እርም ያደረገው በሚደፈርበት መልኩ መጥፎን ስራ ለመስራት በነፍሱ ቢያስብና ቢቆርጥ ይህን ሊያደርግ የቆረጠው በየመን ከሚገኘው የዓደን ከተማ ሆኖ ቢሆንና ባይሰራው እንኳ በዚህ ምክንያት አላህ በአሳማሚ ቅጣቱ ሊቀጣው የተገባ ይሆናል። ለዚህ ቅጣት ማሰቡ ብቻ በቂ ነው።"
03
Benefits
ሐረም ልዩ ስፍራና የላቀ መሆኑን መገለፁ እንረዳለን።
ሰዕዲይ እንዲህ ብለዋል: "በዚህች በተከበረች አንቀፅ ሐረምን ማክበርና እጅግ ማላቅ ግዴታ መሆኑን፤ እንዲሁም ሐረም ውስጥ ሆኖ ወንጀል ማሰብና መስራት መከልከሉን እንረዳለን።"
ዶሐክ እንዲህ ብለዋል: "ሰውዬው ሌላ ምድር ላይ ሆኖ መካ ላይ ወንጀል ለመስራት ቢያስብና ግን ወንጀሉን ባይሰራው እንኳ በርሱ ላይ ወንጀል ይፃፍበታል።"
ሰዕዲይ እንዲህ ብለዋል: "በዚህች በተከበረች አንቀፅ ሐረምን ማክበርና እጅግ ማላቅ ግዴታ መሆኑን፤ እንዲሁም ሐረም ውስጥ ሆኖ ወንጀል ማሰብና መስራት መከልከሉን እንረዳለን።"
ዶሐክ እንዲህ ብለዋል: "ሰውዬው ሌላ ምድር ላይ ሆኖ መካ ላይ ወንጀል ለመስራት ቢያስብና ግን ወንጀሉን ባይሰራው እንኳ በርሱ ላይ ወንጀል ይፃፍበታል።"
Attribution
[رواه أحمد والحاكم]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

